በዳሸን ባንክ የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ላይ ውይይት እየተካሄደ ነው
ዳሸን ባንክ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ባስመዘገባቸው ዝርዝር የስራ አፈፃፀሞች ላይ የባንኩ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እየተወያዩ ነው።
በዚህ የበጀት አመት የግማሽ አመት አፈፃፀም ላይ ውይይት በተካሄደበት ወቅት በሶስተኛው ሩብ አመት በተለየ መልኩ እንዲተገበሩ በታቀዱ ስራዎች አፈፃፀም ውይይቱ ተጀምሯል።
የባንኩ አጠቃላይ የዘጠኝ ወራት ሪፖርት የቀረበ ሲሆን በሪፖርቱ ላይ ያተኮረ ውይይትም እየተካሄደ ነው።
ለሁለት ቀናት በሚቆየው ውይይት በቀሪዎቹ የበጀት ዓመቱ ወራት ባንኩ ያስቀመጣቸውን ዕቅዶች በማሳካት አመታዊ ዕቅዱን እውን ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ውይይት ይካሄዳል።
