ዳሸን ባንክ በጎፋ ዞን በደረሰው የመሬት መንሸራተት ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች 10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አበረከተ ዳሸን ባንክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች ድጋፍ እንዲውል የ10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አበርክቷል። የዳሸን ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ተወካይና ቺፍ ባንኪንግ ኦፕሬሽንስ ኦፊሰር አቶ ጥበቡ ሰለሞን ዳሸን ባንክ በዞኑ ነዋሪዎች ላይ በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን በድጋሚ ገልፀው ባንኩ የአካባቢውን ነዋሪዎች ለመርዳት በሚደረገው አገራዊ ጥረት የበኩሉን ድጋፍ ለማቅረብ ስፍራው ድረስ መገኘቱን አመልክተዋል። ዳሸን ባንክ ተጎጂዎችን በዘላቂነት ለማቋቋም በሚደረገው ጥረትም የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግ አቶ ጥበቡ ገልጸዋል። የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ አጌና ድጋፉን ይዘው በስፍራው ለተገኙ የዳሸን ባንክ ከፍተኛ አመራሮች አደጋው ስላደረሰው ጉዳት ገለፃ ከሰጡ በኋላ ዳሸን ባንክ በአካባቢው ከሚገኘው ቅርንጫፍ ጀምሮ ላበረከተው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ከዳሸን ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ተወካይና ቺፍ ባንኪንግ ኦፕሬሽንስ ኦፊሰር አቶ ጥበቡ ሰለሞን በተጨማሪ የባንኩ ቺፍ ስትራቴጂ ኦፊሰር አቶ ኤልያስ ሁሴን፣ የዳሸን ባንክ ማርኬቲንግ እና ብራንዲንግ ዳይሬክተር አቶ እንዳለ ገብረስላሴ፣ የባንኩ የወላይታ ቀጠና ጽህፈት ቤት ዳይሬክተር አቶ ታዲዮስ ተስፋዬ እና የባንኩ የአርባምንጭ አካባቢ ስራ አስኪያጅ አቶ አማኑኤል አለማየሁ ተገኝተው ድጋፉን አበርክተዋል። Latest Updates ዳሸን ባንክ የተሳተፈበት ግራንድ ኢትዮ ኢድ ኤክስፖ ተከፈተ Mar 19, 2025read more Thousand participate in 5km Women First Run “Dashen Bank Continues as Sole Bank Partner Mar 17, 2025read more Dashen Bank Hosts Grand Iftar to Celebrate Ramadan. Mar 12, 2025read more ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (ማርች-8) በሴቶች ብቻ አገልግሎት በሚሰጠው ዳሸን ኖክ ቅርንጫፍ በድምቀት ተከበረ Mar 8, 2025read more ዳሸን ባንክ ከ22 ሚሊየን ብር በላይ ለግብረ-ሠናይ ድርጅቶች ለገሰ Feb 27, 2025read more
Thousand participate in 5km Women First Run “Dashen Bank Continues as Sole Bank Partner Mar 17, 2025read more