ዳሸን ባንክ በጎፋ ዞን በደረሰው የመሬት መንሸራተት ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች 10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አበረከተ ዳሸን ባንክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች ድጋፍ እንዲውል የ10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አበርክቷል። የዳሸን ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ተወካይና ቺፍ ባንኪንግ ኦፕሬሽንስ ኦፊሰር አቶ ጥበቡ ሰለሞን ዳሸን ባንክ በዞኑ ነዋሪዎች ላይ በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን በድጋሚ ገልፀው ባንኩ የአካባቢውን ነዋሪዎች ለመርዳት በሚደረገው አገራዊ ጥረት የበኩሉን ድጋፍ ለማቅረብ ስፍራው ድረስ መገኘቱን አመልክተዋል። ዳሸን ባንክ ተጎጂዎችን በዘላቂነት ለማቋቋም በሚደረገው ጥረትም የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግ አቶ ጥበቡ ገልጸዋል። የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ አጌና ድጋፉን ይዘው በስፍራው ለተገኙ የዳሸን ባንክ ከፍተኛ አመራሮች አደጋው ስላደረሰው ጉዳት ገለፃ ከሰጡ በኋላ ዳሸን ባንክ በአካባቢው ከሚገኘው ቅርንጫፍ ጀምሮ ላበረከተው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ከዳሸን ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ተወካይና ቺፍ ባንኪንግ ኦፕሬሽንስ ኦፊሰር አቶ ጥበቡ ሰለሞን በተጨማሪ የባንኩ ቺፍ ስትራቴጂ ኦፊሰር አቶ ኤልያስ ሁሴን፣ የዳሸን ባንክ ማርኬቲንግ እና ብራንዲንግ ዳይሬክተር አቶ እንዳለ ገብረስላሴ፣ የባንኩ የወላይታ ቀጠና ጽህፈት ቤት ዳይሬክተር አቶ ታዲዮስ ተስፋዬ እና የባንኩ የአርባምንጭ አካባቢ ስራ አስኪያጅ አቶ አማኑኤል አለማየሁ ተገኝተው ድጋፉን አበርክተዋል። Latest Updates ዳሸን ባንክ በአጋርነት ያዘጋጀው የአፍሪካ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል May 8, 2026read more ሸሪክ ከደንበኞቹ በአደራ መልክ የሰበሰበውን ከ16 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረገ May 2, 2026read more በዳሸን ባንክ የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ላይ ውይይት እየተካሄደ ነው Apr 28, 2026read more የዳሸን ኤክስፖ ሶስተኛ ቀኑን ያስቆጠረ ሲሆን ፣ በዛሬው ዕለት የኮርፖሬት ደንበኞች ትስስር ቀን በሚል የተለያዩ መርሐ-ግብሮች እየተካሄደ ይገኛል። Apr 25, 2026read more ባንኩ በቅርቡ ይፋ ያደረጋቸው አገልግሎቶችን በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የማስተዋወቅ ስራ ተከናወነ Apr 25, 2026read more
የዳሸን ኤክስፖ ሶስተኛ ቀኑን ያስቆጠረ ሲሆን ፣ በዛሬው ዕለት የኮርፖሬት ደንበኞች ትስስር ቀን በሚል የተለያዩ መርሐ-ግብሮች እየተካሄደ ይገኛል። Apr 25, 2026read more