ዳሸን ባንክ በጎፋ ዞን በደረሰው የመሬት መንሸራተት ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች 10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አበረከተ ዳሸን ባንክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች ድጋፍ እንዲውል የ10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አበርክቷል። የዳሸን ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ተወካይና ቺፍ ባንኪንግ ኦፕሬሽንስ ኦፊሰር አቶ ጥበቡ ሰለሞን ዳሸን ባንክ በዞኑ ነዋሪዎች ላይ በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን በድጋሚ ገልፀው ባንኩ የአካባቢውን ነዋሪዎች ለመርዳት በሚደረገው አገራዊ ጥረት የበኩሉን ድጋፍ ለማቅረብ ስፍራው ድረስ መገኘቱን አመልክተዋል። ዳሸን ባንክ ተጎጂዎችን በዘላቂነት ለማቋቋም በሚደረገው ጥረትም የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግ አቶ ጥበቡ ገልጸዋል። የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ አጌና ድጋፉን ይዘው በስፍራው ለተገኙ የዳሸን ባንክ ከፍተኛ አመራሮች አደጋው ስላደረሰው ጉዳት ገለፃ ከሰጡ በኋላ ዳሸን ባንክ በአካባቢው ከሚገኘው ቅርንጫፍ ጀምሮ ላበረከተው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ከዳሸን ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ተወካይና ቺፍ ባንኪንግ ኦፕሬሽንስ ኦፊሰር አቶ ጥበቡ ሰለሞን በተጨማሪ የባንኩ ቺፍ ስትራቴጂ ኦፊሰር አቶ ኤልያስ ሁሴን፣ የዳሸን ባንክ ማርኬቲንግ እና ብራንዲንግ ዳይሬክተር አቶ እንዳለ ገብረስላሴ፣ የባንኩ የወላይታ ቀጠና ጽህፈት ቤት ዳይሬክተር አቶ ታዲዮስ ተስፋዬ እና የባንኩ የአርባምንጭ አካባቢ ስራ አስኪያጅ አቶ አማኑኤል አለማየሁ ተገኝተው ድጋፉን አበርክተዋል። Latest Updates ሴቶች አቅማቸውን አውጥተው እንዲጠቀሙ ባንኩ ድጋፉን እንደሚቀጥል ገለጸ Mar 7, 2026read more Ries Engineering S.Co Congratulates Dashen Bank on Its 30th Anniversary Mar 4, 2026read more Avon Industries PLC Extends Congratulations to Dashen Bank on Its 30th Anniversary Mar 4, 2026read more Executive Management of Hibret Bank Extends Congratulatory Message to Dashen Bank Feb 28, 2026read more EthSwitch S.C. Honors Dashen Bank’s 30th Anniversary Feb 27, 2026read more
Avon Industries PLC Extends Congratulations to Dashen Bank on Its 30th Anniversary Mar 4, 2026read more
Executive Management of Hibret Bank Extends Congratulatory Message to Dashen Bank Feb 28, 2026read more