ዳሸን ባንክ ብቸኛ የባንክ አጋር የሆነበት ሐዋሳ ግማሽ ማራቶን በሃዋሳ ከተማ ለ14ኛ ጊዜ በድምቅት ተካሄደ
ዳሸን ባንክ ብቸኛ የውድድሩ የባንክ አጋር የሆነበት እና ለ14ኛ ግዜ በሃዋሳ ከተማ የተደረገው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የ8 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ በዛሬው ዕለት በድምቀት ተካሄደ ።
ውድድሩን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ዳሸን ባንክ ባዘጋጀው ልዩ መድረክ ላይ የባንኩ የተለያዩ አገልግሎቶቹን በተለይም ዳሸን ሱፐር አፕን ለተሳታፊዎች አስተዋውቋል ።
በውድድሩ መርሃ-ግብር ላይ እድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ለአሸናፊ ተወዳዳሪዎች በዳሸን ባንክ የሃዋሳ ቀጠና ጽ/ቤት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አስናቀ ደምሴ አማካኝነት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል ።
የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ብቸኛ የባንክ አጋር ሆኖ ለረዥም ጊዜ አጋር የሆነው ዳሸን ባንክ አዲስ አበባ የሚካሄደውን ጨምሮ በተለያዩ የሀገራችን ከተሞች ላይ በሚደረጉ ውድድሮች በመሳተፍ ከሚሰጠው የባንክ ዘርፍ አገልግሎት ባሻገር በስፖርታዊ እንቅስቃሴ ህብረተሰቡ እራሱን እንዲያደበርና ጤናው እንዲጠበቅ የበኩሉን አስተዋጽዖ በማበርከት ላይ ይገኛል ።
በቀጣይም የ2018 ዓ.ም “ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ” በጅማ፣በቆጂ፣በአርባምንጭ እና በሐረር ተመሳሳይ ውድድር ይካሄዳል።
