Select Page

ዳሸን ባንክ ብቸኛ የባንክ አጋር የሆነበት የቡና ዐውደ-ርዕይ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።

ዳሸን ባንክ ብቸኛ የባንክ አጋር የሆነበት የቡና ዐውደ-ርዕይ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።

የዐውደ-ርዕዩ ተሳታፊዎች ግብይት በሚፈጽሙት ወቅት የተቀላጠፈ አገልግሎት እየሰጠ እንደሆነም የዳሸን ባንክ አንድነት ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አቶ ሳሙኤል ብርሐኑ ተናግረዋል ።

ባንኩ  በትላልቅ ሐገራዊ ፕሮጀክቶች ላይ የራሱን አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሆነ የሚያነሱት አቶ ሳሙኤል የቡና ወጭ ንግድ ዘርፍ ደግሞ አንዱ እንደሆነ አመላክተዋል።

በዐውደ-ርዕዩ ላይ ቡና ዘርፍ ላይ ለተሰማሩ ተቋማት ባንኩ አጋር መሆኑን የሚያሳይበት መድረክ እንደሆነም አብራርተዋል ።

የዐውደ-ርዕዩ ተሳታፊ የሆነው ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የአግሮ ክላስተር ዘርፍ ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ፈለቀ ታደሰ በበኩላቸው የቡና መገኛ ሐገር እንደመሆናችን ዘርፉን ለማነቃቃት መስራት ይገባናል ተብለዋል ።

ዐውደ- ርዕዩ ይህን ሐሳብ የሚደግፍ በመሆኑ የሚበረታታ ነው ያሉት አቶ ፈለቀ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በመስኩ ያለውን ጉልህ አበርክቶ እንደሚያስቀጥል አስረድተዋል።

በዐውደ-ርዕዩ ላይ ቡናን እሴት ጨምሮ መላክና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዩች ዙሪያ የፓናል ውይይት ተደርጓል። በውይይቱ ዳሸን ባንክን ወክለው የባንኩ ኮርፓሬት ባንኪንግ ዘርፍ ዳይሬክተር አቶ ደጀኔ ግርማ  ተሳትፈዋል።

 

Facebook
Twitter
YouTube
LinkedIn
Instagram
Telegram