Select Page

ዳሸን ባንክ አጋር የሆነበት የቡና አውደ-ርዕይ ተከፈተ

ዳሸን ባንክ አጋር የሆነበት የቡና አውደ-ርዕይ (Coffee Feast) በዛሬው ዕለት በሸራተን አዲስ ሆቴል ተከፍቷል።

በአውደ-ርዕዩ ላይ ቡና ላይ የተሰማሩ ተቋማት ምርትና አገልግሎታቸውን አቅርበዋል።

ዳሸን ባንክ በአውደ-ርዕዩ ላይ የተሟላ የባንክ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ሲሆን፤ ተሳታፊዎች ዳሸን ሱፐር አፕ መተግበሪያን በመጠቀም በቀላሉ ግብይታቸውን እየፈጸሙ ይገኛሉ።

የአውደ-ርዕዩ ተሳታፊዎች ዳሸን ባንክ በአጋርነት እየሰራ መሆኑ ግብይታቸውን በቀላሉ ለማቀላጠፍ እንዳገዛቸው ገልጸዋል።

ዛሬ ኅዳር 13/2018 ዓ.ም በይፋ በተከፈተው አውደ-ርዕይ ላይ በቡና ዘርፍ ላይ የሚታዩ አበረታች ውጤቶችና እያጋጠሙ የሚገኙ ተግዳሮቶችን በተመለከተ የፓናል ውይይት እየተደረገ ይገኛል።

አውደ ርዕዩ እስከ ነገ እሑድ ኅዳር 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይቀጥላል።

 

Facebook
Twitter
YouTube
LinkedIn
Instagram
Telegram