ዳሸን ባንክ ከኤግል ላየን ቴክኖሎጂ ጋር በመተባበር ከወለድ-ነጻ የዱቤ አገልግሎት ማግኘት የሚያስችል “ከወለድ-ነጻ ዱቤ አለ” አገልግሎትን አስተዋወቀ፡፡
ከወለድ-ነጻ ዱቤ አለ “IFB DubeAle” የሸሪዐህ መርሆዎችን ተከትሎ የሚሰራ አገልግሎት ሲሆን እንደ ሽያጭ ውል የሚሰራና በደንበኛው ጥያቄ መሰረት የዱቤ አገልግሎት የሚያገኝበት አሰራር ነው ፡፡
ስለ አገልግሎቱ ማብራሪያ የሰጡት የዳሸን ባንክ ዋና ስራ አስፈጻሚ ተወካይና ቺፍ ባንኪንግ ኦፕሬሽን ኦፊሰር አቶ ጥበቡ ሰለሞን በባንኩ ከወለድ-ነጻ ሂሳብ ያለው ደንበኛ አገልግሎቱን መጠቀም እንደሚችል አስረድተዋል፡፡
ባንኩ አዳዲስ አገልግሎቶችን የማስተዋወቅ ጥረቱን በመቀጠል አሁንም ከኤግል ላየን ቴክኖሎጂስ ጋር በመተባበር የቆየውን የማህበረሰባችንን የዱቤ ግብይት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እና አስተማማኝ የባንክ አሰራር በማገዝ “ከወለድ-ነጻ ዱቤ አለ” የተሰኘና ሸማቾች በዱቤ በፈለጉት ጊዜ ያሻቸውን ገዝተው ቆይተው ከወለድ-ነጻ በሆነ መንገድ መክፈል የሚችሉበትን አሰራር እንዳስተዋወቀም ተመላክቷል፡፡
በተጨማሪም ደምበኛው ቋሚ ንብረት ካለው እንደ ዋስትና ማስያዥያ አልያም የሶስተኛ ወገን ዋስትና ማቅረብ ይችላል። ደምበኛው በባንኩ ተቀማጭ ገንዘብ ካለው ጥሬ ገንዘብ (በዉጭ ምንዛሬ ወይም በብር) ዋስትና ማስያዝ እንደሚችልም ተብራርቷል።
ዳሸን ባንክ አሁን ላይ ባስተዋወቀው “ከወለድ ነጻ-ዱቤ አለ አገልግሎት” ደንበኞች እስከ 700,000.00 (ሰባት መቶ ሺህ ብር) ድረስ ያሻቸውን መሸመት ያስችላቸዋል፡፡
ከወለድ ነጻ ዱቤ አለ ተጠቃሚዎች ዛሬ ለገዙት በሸሪዓህ ህግ የተፈቀዱ ምርትና አገልግሎቶች ክፍያውን ወደፊት የሚከፍሉ ሲሆን አከፋፈሉም እንደ ደንበኛው ምርጫ በ3 ወር፣በ6 ወር እና በ12 ወር ይሆናል፡፡
Other Photo Albums

ዳሸን ባንክ 6.4 ቢሊየን ብር ትርፍ አስመዘገበ

ዳሸን ባንክ የ6ኛውን የታማኝ የግብር ከፋዮች ሽልማት የፕላቲኒየም ደረጃ ተሸላሚ ሆነ

Dashen Bank Culture Club 2017 EC Events Calendar Unveiled!

Dashen Bank Participates in NBE’s Launch of DEBO Initiative to Boost Remittances

ዳሸን ባንክ ከኤግልላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ እና ከማስተር ካርድ ጋር በመተባበር ያቀረበው “ጌትፊ ፔይ ባይ ሊንክ” (GetFee – Pay By Link) የተሰኘ የኦንላየን የክፍያ አማራጭ አገልግሎት አስተዋወቀ፡፡

የዳሸን ባንክ 28ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እና የሠራተኞች ቀን

ሶስቱ ጓደኛማቾች የዳሸን ከፍታ ውድድርን አሸነፉ!

ዳሸን የ“ዘ ባንከር” ሽልማትን ለ13ኛ ጊዜ አሸነፈ

ዳሸን ባንክ የአለም አቀፉ አነስተኛና መካከለኛ ተቋማት ፋይናንስ ፎረም አባል ሆነ

ዳሸን ባንክ፣ የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደርና የከተማው የንግድና ዘርፍ ማህበራት ም/ቤት የሶስትዮሽ ስምምነት ተፈራረሙ

ዳሸን ባንክ 18 ቢሊዮን ብር ገቢ አስመዘገበ

ዳሸን ባንክ የ2015 የባንኮች የእግር ኳስ ውድድር ዋንጫ አሸነፈ

ዳሸን ባንክና ማስተርካርድ የመጀመሪያውን ቨርቹዋል አለም አቀፍ ቅድመ ክፍያ ካርድ አስተዋወቁ::

ዳሸን ባንክ በቴክኖሎጂ የታገዘ የዱቤ ግብይት አስተዋወቀ

Donation to Somali Regional State

Dashen American Express International card Inaguration

28th Ordinary & 25th Extra Ordinary Annual Shareholder Meeting at Mechare Meda

The 27th Ordinary and 24th Extra Ordinary General Meeting of Shareholders of Dashen Bank

ዳሽን ባንክ የ 10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ለኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝ መከላከያ ዝግጅት አበረከተ
