Select Page
ለዳሸን ባንክ አ.ማ ባለአክስዮኖች በሙሉ

ለዳሸን ባንክ አ.ማ ባለአክስዮኖች በሙሉ

ለዳሸን ባንክ አ.ማ ባለአክስዮኖች በሙሉ

የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አስመራጭ ኮሚቴ የዕጩ አባላትን ጥቆማ ከመጋቢት 23 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እየተቀበለ መሆኑ ይታውቃል። ስለሆነም ለባንኩ ዳይሬክተሮች ቦርድ አባልነት መስፈርቱን የሚያሟሉ ዕጩዎችን እስከ ሰኔ 23 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ መጠቆም የምትችሉ ሲሆን ስለተጠቋሚዎች መስፈርት እና ሌሎች ዝርዝር መረጃዎች ከባንኩ ድረ-ገፅ www.dashenbanksc.com እንዲሁም መጋቢት 20 ቀን 2015 ዓ.ም ከወጡት ሪፖርተር አማርኛው እና አዲስ ዘመን ጋዜጦች ማግኘት የሚቻል መሆኑን እየገለፀ፤ የጥቆማ ማቅረቢያ ቅፁን ከሁሉም የባንኩ ቅርንጫፎች፤ ከባንኩ ዋና መ/ቤት የዳይሬክተሮች ቦርድ አስመራጭ ኮሚቴ ጊዜያዊ ጽ/ቤት እና ከባንኩ ድረ ገፅ ማግኘት የሚቻል መሆኑን በአክብሮት ያሳውቃል፡፡

ማሳሰቢያ፡ የጥቆማ መስጫ ወረቀቱ በፖስታ ታሽጎ በአቅራቢያ ላሉ የባንኩ ቅርንጫፎች ወይም ባንኩ ዋና መስሪያ ቤት 14ተኛ ፎቅ ላይ ለሚገኘው የአስመራጭ ኮሚቴው ጊዜያዊ ፅ/ቤት ሊመለስ የሚገባ ሲሆን ከሰኔ 23 ቀን 2015 ዓ.ም በኋላ ጥቆማ ለማቅረብ የሚቀርብ ጥያቄም ሆነ ከዚህ ጊዜ በኋላ ባንኩ ጋር የሚደርስ የጥቆማ መስጫ ወረቀት ተቀባይነት የሌለው መሆኑን በአክብሮት ያሳውቃል፡፡

ለዳሸን ባንክ አ.ማ ባለአክስዮኖች

ለዳሸን ባንክ አ.ማ ባለአክስዮኖች

ለዳሸን ባንክ አ.ማ ባለአክስዮኖች

ዕጩ ዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ጥቆማ ከመጋቢት 23ቀን 2015 ዓ.ም እስከ ሰኔ 23ቀን 2015ዓ.ም ድረስ የሚከናወን ስለሆነ የጥቆማ ፎርሙን ከሁሉም የዳሸን ባንክ ቅርንጫፎች ወይንም ከስር ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ጥቆማ እንድታቀርቡ እናሳውቃለን፡፡

የጥቆማ ፎርም

የጥቆማ ፎርም

 

VISA, Mastercard and Amex card holders can now donate to Ethiopian Red Cross Society online

VISA, Mastercard and Amex card holders can now donate to Ethiopian Red Cross Society online

VISA, Mastercard and Amex card holders can now donate to Ethiopian Red Cross Society online

We have finished integration with Ethiopian Red Cross Society that enable people to donate from all over the world. Any one who have VISA, Mastercard and Amex card can donate online by using the link https://donation.dashenbanksc.com/redcross/ or to Dashen bank account number 907.

ዳሸን ባንክ ከ5 ቢሊየን ብር በላይ ከወለድ ነፃ ፋይናንስ አቀረበ

ዳሸን ባንክ ከ5 ቢሊየን ብር በላይ ከወለድ ነፃ ፋይናንስ አቀረበ

ዳሸን ባንክ ከ5 ቢሊየን ብር በላይ ከወለድ ነፃ ፋይናንስ አቀረበ

ዳሸን ባንክ በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ሸሪክ የተሰኘ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት በማስተዋወቅ አገልግሎት የጀመረው ከ5 ዓመት በፊት ነበር፡፡ ይህም ባንኩ በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች አካታች መሆኑን ያሳየበት ሆኗል፡፡

ይህ የባንክ አገልግሎት የዛሬ አምስት ዓመት ሲጀመር በዘርፉ በቂ ልምድና ክህሎት የሌለ በመሆኑ ከፍተኛ ዝግጅት የጠየቀ ነበር፡፡ የራሱ የሆኑ የፖሊሲና አሰራር ማዕቀፎችና ማዘጋጀትና መዘርጋት፣ በዘርፉ የሚሰማራውን የሰው ሃይል ማብቃት የአገልግሎቱን ልዩ ምልክት ማዘጋጀትና ሌሎችም የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን  ባንኩ ሰፊ ጊዜ ወስዶ አከናውኗቸዋል፡፡

ይህም ምንም እንኳን በዘርፉ የሚሰጠው አገልግሎት አዲስና አጭር ዕድሜ ያለው ቢሆንም ዳሸን ባንክ በአጭር ጊዜ ተቀባይነቱን በማስፋት በርካታ ስኬቶችን እንዲያስመዘግብ አስችሎታል፡፡ ዳሸን ባንክ አገልግሎቱን የጀመረው ራሱን የቻለ የሸሪዓ አማካሪ ምክር ቤት በማቋቋም ነበር፡፡

ከአምስት ዓመታት በፊት በአንድ መስኮት መሰጠት የተጀመረው ይህ አገልግሎት ዛሬ ላይ ከፍተኛ ዕድገት በማሳየት በ62 ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አግልግሎት በሚሰጡ ቅርንጫፎች አገልግሎት በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ 700 በሚሆኑ ቅርንጫፎች በአንድ መስኮት አገልግሎቱ በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡ ዛሬ ላይ የዳሸን ሸሪክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ከ600 ሺ በላይ የሆኑ ሲሆን ባንኩ ከ7 ቢሊየን ብር በላይ ተቀማጭ ገንዘብ ማሰባሰብ ችሏል፡፡

ዳሸን ባለፉት 5 ዓመታት በዚህ ዘርፍ ብቻ በተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች ለተሰማሩ ደንበኞቹ ከ5 ቢሊየን ብር በላይ ማበደር ችሏል፡፡ ባለፈው ዓመት ብቻ ባንኩ በዚህ ዘርፍ የሰጠው የብድር መጠን ከ4.3 ቢሊየን ብር በላይ የነበር ሲሆን ይህም ከቀደመው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ92.3 በመቶ ዕድገት ያሳየ ነበር፡፡

ባንኩ በዘርፉ ተደራሽነቱንና አካታች አገልግሎቶችን ከመስጠት አልፎ ዘርፉ የሚጠይቀውን ስነ-ምግባር ተግባራዊ በማድረግ ተጠቃሽ ሚና ተጫውቷል፡፡  ወደፊትም ባንኩ ማህበረሰባችንን ከአገልግሎቱ ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያደገውን ርብርብ አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡

 

ዳሽን ባንክና ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ያስገነቡት የምገባ ማዕከል  ተመረቆ ሥራ ጀመረ

ዳሽን ባንክና ሜድሮክ ኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ግሩፕ  ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጋራ በመተባበር በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ቦሌ አራብሳ ኮንዶሚኒየም አካባቢ  በ25 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነቡት ተስፋ ብርሃን አሙዲ  3ኛ ቅርንጫፍ የምገባ ማዕከል የካቲት 24 ቀን 2015 ዓ.ም በይፋ ተመርቆ ሥራ ጀምሯል፡፡

በምርቃው ሥነ-ስርዓት ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አባቤ እንደገለጹት የከተማ አስተዳደሩ ትኩረት ሰጥቶ ከሚሰራቸው  ሰው ተኮር  የልማት ሥራዎቸ  መካከል በከተማዋ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች   ምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ በተመረጡ የከተማዋ ቦታዎች ምገባ ማዕከላት ማቋቋም ነው፡፡ በዚሁ መሰረት  ዳሽን ባንክና ሜድሮክ ኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ግሩፕ  ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጋራ በመተባበር ተስፋ ብርሃን አሙዲ ቅርንጫፍ የተሰኘ የምገባ ማዕከልን በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ  ግንብቶ ለፍሬ በማብቃት  በተለያዩ ምክንያቶች የተፈናቀሉና በአሁኑ ጊዜ ለከፋ ችግር የተጋለጡ  የአካባቢው ነዋሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡

 ማዕከሉ በአካባቢው ለሚኖሩ 30 ሴቶች ቋሚ የሥራ እድል እንደሚፈጥም  ከንቲባዋ ጠቁመዋል፡፡

የሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል  መሀመድ በበኩላቸው ድርጅታቸው ከዳሻን ባንክ ጋራ በመተባበር ቀደም ብሎ ሁለት የምገባ ማእከላትን በአዲስ ከተማና በልደታ ክፍለ ከተማ በመገንባት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረጉን አስታውሰው አሁን በለሚ ኩራ የተገነባውን ተሰፋ ብርሃን  አሙዲ ቅርንጫፍ የምገባ ማዕከል ግንብቶ ከማጠናቀቅ በተጨማሪም በየአመቱ ለምገባ የሚወጣውን 25 ሚሊዮን ብር የሚሆን  ወጪ  ድርጅታቸው ከዳሽን ባንክ ጋር በመሆን ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡ በዕለቱ ዳሽን ባንክ ለምገባ ማዕከሉ ግንባታ ለአበረከተው አስተዋጽኦ የዕውቅና ሽልማት ተበርክቶለታል፡፡

 

ዳሸን ባንክ በቴክኖሎጂ የታገዘ የዱቤ ግብይት አስተዋወቀ

ዳሸን ባንክ በቴክኖሎጂ የታገዘ የዱቤ ግብይት አስተዋወቀ

ዳሸን ባንክ በቴክኖሎጂ የታገዘ የዱቤ ግብይት አስተዋወቀ

(አዲስ አበባ፡ ታህሳስ 25፤2015) ዳሸን ባንክ በቴክኖሎጂ የታገዙ አገልግሎቶችን በማስተዋወቅ በሚሊየን የሚቆጠሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የባንክ አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡

ባንኩ አዳዲስ አገልግሎቶችን የማስተዋወቅ ጥረቱን በመቀጠል አሁንም ከኤግል ላየን ቴክኖሎጂስ ጋር በመተባበር የቆየውን የማህበረሰባችንን የዱቤ ግብይት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እና አስተማማኝ የባንክ አሰራር በማገዝ ዱቤ አለ የተሰኘና ሸማቾች በዱቤ በፈለጉት ጊዜ ያሻቸውን ገዝተው ቆይተው መክፈል የሚችሉበትን አሰራር እና መተግበሪያ ጥር 02 ቀን 2015 ዓ.ም. በሸራተን አዲስ ሆቴል አስመርቋል፡፡

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የዳሸን ባንክ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አስፋው ዓለሙን ጨምሮ በርካታ የንግድ ማህበረሰቡ ተገኝተዋል፡፡

ይህ አገልግሎት ዳሸን ባንክ ከተለያዩ የንግድ ተቋማት ጋር በመተባበር ህብረተሰቡ ቋሚና አላቂ ዕቃዎችንና በርካታ አገልግሎቶችን በ3 ወር፣ በ6 ወርና በ12 ወር በሚመለስ ዱቤ በወለድና ያለወለድ መግዛት የሚያስችል አማራጭ ነው፡፡ ይህም የማህበረሰባችንን የኑሮ ጫና ይቀንሳል፤ በገበያው ውስጥ ምርት እንዲገላበጥ፣ አገልግሎቶችም ይበልጥ ጥቅም ላይ እንዲውሉ እና የንግድ ማህበረሰቡ ሽያጭ እንዲያድግ ብሎም ኢኮኖሚው እንዲነቃቃ ጉልህ ድርሻ ይኖረዋል፡፡

ዱቤ አለ የምርትና አገልግሎት አቅራቢዎች ለደንበኞቻቸው እጅግ አመቺ የሆነ የዱቤ አገልግሎት በማቅረብ ተመራጭነታቸውን እንዲያሳድጉም ይረዳል፡፡

ደንበኞች መተግበሪያውን ከፕሌይ ስቶር ወይም ከአፕ ስቶር በማውረድ ለአገልግሎቱ መመዝብ ይችላሉ፡፡ ከተመዘገቡ በኋላም ወደ ዳሸን ባንክ ቅርንጫፍ በማምራት የዱቤ ገደብ ማስፈቀድና የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን ይችላሉ፡፡

ዳሸን ባንክ ጠንካራ የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት መገንባት የቻለ ሲሆን በቅርቡ በግል ባንኮች ታሪክ የመጀመሪያው ትልቅና ዘመናዊ የሆነውን የመረጃ ማዕከል አስመርቋል፡፡ በዚህ ጠንካራ መሰረተ ልማት ላይ ተንተርሶም አሞሌ በተሰኘው የዲጂታል ባንክ አገልግሎቱ ሰፊውን የማህበረሰባችን ክፍል ተጠቃሚ አድርጓል፡፡ በቅርቡም አነስተኛ ቁጠባና ብድር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር መጀመሩ ይታወሳል፡፡

 

(more…)

Facebook
Twitter
YouTube
LinkedIn
Instagram
Telegram