Select Page
ዳሸን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት “ሸሪክ“የጀመረበትን 6ተኛ አመት በድምቀት አከበረ

ዳሸን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት “ሸሪክ“የጀመረበትን 6ተኛ አመት በድምቀት አከበረ

ዳሸን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት “ሸሪክ“የጀመረበትን 6ተኛ አመት በድምቀት አከበረ

(አዲስ አበባ- የካቲት 29 ቀን 2016 ዓ.ም) ዳሸን ባንክ ሸሪክ የተሰኘ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት የጀመረበትን 6ተኛ አመት ባከበረበት ዕለት ከደንበኞች በበጎ አደራጎት ፈንድ በአደራ የሰበሰበውን 12.5 ሚሊዮን ብር ለ18 አገር በቀል የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ድጋፍ አደረገ፡፡

ዳሸን ባንክ በሚሰጠዉ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ብቻ አሁን ላይ ከ1 ሚሊየን በላይ ደንበኞችን ማፍራት ችሏል፡፡ ይህንንም በተለያዩ ስነ-ስርዓቶች አክብሯል፡፡

የዳሸን ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ዓለሙ በስነ-ስርዓቱ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ለባንኩ አመኔታቸውን ለሰጡ ደንበኞች ከፍ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበው ወደፊትም ለላቀ ስኬት የሸሪዓህ መርህን በመከተል አዳዲስ የባንክ አገልግሎቶቸን እንደሚያቀርብ ገልፀዋል፡፡

አቶ አስፋው አክለውም በእለቱ በአደራ የተሰጣቸውን ገንዘብ የተረከቡ 18 አገር በቀል በጎ አድራጎት ድርጅቶች የማህበረሰቡን ችግር ለመቅረፍ በሚያስችሉ ስራዎች ላይ እንዲያውሉት አደራ ብለዋል፡፡ በቀጣይም ባንኩ እነኚህንም ሆነ መሰል ሌሎች ተቋማት የማህበረሰቡን ችግሮች በዘላቂነት በሚፈቱ ስራዎች ላይ በጋራ ለመስራት የሚሻ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ዳሸን ባንክ የካቲት 26 ቀን 2010 ዓ.ም በአንድ መስኮት መስጠት የጀመረው አገልግሎት አድጎ ዛሬ ላይ ከ70 በላይ ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት በሚሰጡ ቅርንጫፎች እንዲሁም ከ800 በላይ በሆኑ ቅርንጫፎች ደግሞ በመስኮት ለደንበኞቹ የተሟላ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ ከደንበኞቹም ከ9.5 ቢሊየን ብር በላይ ማሰባሰብ የቻለ ሲሆን ከዚህም ውስጥ ከ6 ቢሊየን ብር በላይ በተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ ለተሰማሩ ደንበኞቹ ፋይናንስ አድርጓል፡፡

ባንኩ ከወለድ-ነፃ የባንክ አገልግሎት የሚጠይቀውን ሙያዊና ሸሪዓዊ ስነ-ምግባር ተግባራዊ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ በዚህም ረገድ እ.ኤ.አ ህዳር 28 ቀን 2023 በባህሬን ማናማ በተካሄደው 9ኛው የኢስላሚክ ሪቴል ባንክ ሽልማት ላይ ጠንካራው ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት በኢትዮጵያ የሚሰጥ ባንክ (The strongest Islamik Retail Banking Window in Ethiopia 2025) በሚል ተቀማጭነቱ ሎንዶን በሚገኘውና  በፋናንስ ዘርፍ ጥናትና ምርምር በሚሰራዉ  ኬምብሪጅ አይ ኤፍ ኤ(Cambridge IFA) የተሰኘ ተቋም ሽልማት አግኝቷል፡፡ ባንኩን ለዚህ ሽልማት ከአበቁት መሰፈርቶች አንዱ  ጠንካራ የሸሪዓህ አስተዳደር ማዕቀፍ በመተግበሩ ነው፡፡

ባንኩ በአለም አቀፍ ደረጃ የእስላማዊ ፋይናንስ ተቋማትን የሂሳብ፣ ኦዲት እና ሸሪዓህ መስፈርቶችን የሚያወጣው ተቋም (AAOIFI) ቋሚ አባል የሆነ በኢትዮጳያ ብቸኛው የፋይናንስ ተቋም መሆኑ ይታወቃል፡፡

ሸሪክ የተለያዮ የተቀማጭ እና ኢንቨስትመንት አማራጮችን ይዞ የቀረበ ሲሆን ለአብነት ወዲዓህ(የአደራ ተቀማጭ ሂሳብ)፣ አን-ኒሰዕ ወዲአህ የሴቶች ሂሳብ፣ የሃጅ መንፈሳዊ ጉዞ ለማከናወን ደንበኞች ቁጠባ የሚያደርጉበት ሃጅ ወዲዓህ የቁጠባ ሂሳብ፣  በዉጭ ሃገር ምንዛሬ የሚከፈት ወዲዓህ የቁጠባ ሂሳብ፣ ቀርድ የተንቀሳቃሽ ሂሳብ (የቼክ ሂሳብ) እና የሙዳረባህ የጊዜ ገደብ ተቀማጭ(የኢንቨስትመንት ሂሳብ) ይገኙበታል፡፡

 

አዲሱ የዳሸን ባንክ ቦርድ አቶ ዱላ መኮንንን በድጋሚ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀ-መንበር አድርጎ መረጠ

አዲሱ የዳሸን ባንክ ቦርድ አቶ ዱላ መኮንንን በድጋሚ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀ-መንበር አድርጎ መረጠ

አዲሱ የዳሸን ባንክ ቦርድ አቶ ዱላ መኮንንን በድጋሚ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀ-መንበር አድርጎ መረጠ

አዲስ አበባ፤ የካቲት 08 ቀን 2016 ዓ.ም- የዳሸን ባንክ ባለአክሲዮኖች ባካሄዱት 30ኛው መደበኛ ጉባኤ የተመረጠውና የምርጫውም ውጤት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የፀደቀለት አዲሱ የዳሸን ባንክ ቦርድ ባደረገው የመጀመሪያ ጉባኤ ላይ ባለፉት ሶስት ዓመታት ባንኩን በዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀ-መንበርነት ያገለገሉትን አቶ ዱላ መኮንንን በድጋሚ በዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀ-መንበርነት መርጧል፡፡

አዲሱ ቦርድ የካቲት 05፡ 2016 ዓ.ም በሸራተን አዲስ ሆቴል ባካሄደው ጉባኤ ለቀጣይ ሶስት አመታት ዳሸን ባንክን በዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀ-መንበርነት እንዲያገለግሉ በድጋሜ የመረጣቸው አቶ ዱላ መኮንን በአሁኑ ወቅት የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የማዕድን ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ፡፡

አዲሱ ሊቀመንበር አቶ ዱላ መኮንን የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በኤሌክትሪካል ኢንጅነሪንግ፣ እንዲሁም የማስተርስ ዲግሪያቸውንም በቢዝነስ አስተዳደር ከዚሁ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል፡፡ በአግሪካልቸራል ምህንድስናም ዲፕሎማ አላቸው፡፡

አቶ ዱላ በወንጂ ሸዋ፣ መተሃራ እና ፊንጫ ስኳር ፋብሪካዎች እንዲሁም በሌሎች ተቋማት በአጠቃላይ ለ24 አመታት አገልግለዋል፡፡ በሊሙ ቡና ልማት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ የሰሩት አቶ ዱላ ከዚያ በኋላም የፊንጫ ስኳር ፋብሪካ ዋና ሥራ አስኪያጅም ነበሩ፡፡ የኢትዮ ሌዘር ኢንዱስትሪ ኃ/የተወ/የግል/ኩባንያ ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ ዱላ በሆራይዘን ፕላንቴሽን ኃ/የተወ/የግል/ኩባንያም በከፍተኛ ኃላፊነት ሰርተዋል፡፡

አዲስ የተመረጡት የቦርድ አባላት እና ባንኩን ላለፉት ሶስት ዓመታት ያገለገሉት የቦርድ አባላት የስራ ርክክብ ያደረጉ ሲሆን ንዑስ ኮሚቴዎችንም አዋቅረዋል፡፡ ባንኩ አዲስ ለተመረጡት የቦርድ አባላት አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴውን አስመልክቶ ገለፃ ሰጥቷል፡፡

የዳሸን ባንክ 28ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እና የሠራተኞች ቀን

የዳሸን ባንክ 28ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እና የሠራተኞች ቀን

የዳሸን ባንክ 28ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እና የሠራተኞች ቀን

ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ የአየር ትራንስፖርት ክፍያ አገልግሎት ይፋ አደረጉ

ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ የአየር ትራንስፖርት ክፍያ አገልግሎት ይፋ አደረጉ

ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ የአየር ትራንስፖርት ክፍያ አገልግሎት ይፋ አደረጉ

አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 18 ቀን 2016 ዓ.ም ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደንበኞች የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ተጠቅመው ክፍያውን ቆይተው የሚከፍሉበትን አዲስ የክፍያ አማራጭ በጋራ አስተዋወቁ።

አቶ ዮሃንስ ሚሊዮን የዳሽን ባንክ ዲጂታል ባንኪንግ ዋና መኮንን:‘ጉዞዎ ይቀድማል ክፍያው ይደርሳል’ በሚል የተሰየመው ይህ አገልግሎት በደንበኞች ምርጫ መሰረት በ6 ወር ወይም በ12 ወር የብድር ክፍያ የሚሰጥ መሆኑን አመልክተዋል። ደንበኞች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለመሆን በዳሸን ባንክ የሂሳብ ቁጥር መክፈት እንደሚገባቸው እና በተጨማሪም በባንኩ ቢያንስ ለሶስት ወራት አገልግሎት ያገኙ መሆን እንደሚኖርባቸውም ጠቁመዋል።  

አቶ ዮሃንስ አክለውም አገልግሎቱን ለማግኘት ደንበኞች አቅራቢያቸው ወደሚገኝ የዳሸን ባንክ ቅርንጫፍ በሚያመሩበት ወቅት አስፈላጊ ሰነዶችን ማሟላት የሚገባቸው ሲሆን ማስያዣም ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸውም ገልፀዋል።

ስምምነቱን አስመልክቶ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና የንግድ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ለማ ያዴቻ የሚከተለውን መልዕክት አስተላልፈዋል፣ “የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደንበኛ ተኮር አሰራርን እንደመከተሉ የተለያዩ ዘመናዊ እና ለመጠቀም ቀላል የሆኑ ቴክኖሎጂዎችን እያስተዋወቀ ይገኛል። የምናበለጽጋቸው ቴክኖሎጂዎች ለደንበኞቻችን ምቹ መሆናቸው እንደተጠበቁ ሆኖ የአገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት ጋርም የተጣጣሙ እንዲሆኑ እናደርጋለን። ዛሬም አጋራችን ከሆነው የዳሽን ባንክ ጋር በመተባበር ለደንበኞቻችን ያቀረብነው አዲስ የክፍያ አማራጭ ተግባራዊ እንዲሆን የሞባይል መተግበሪያችን ከአዲሱ የክፍያ አገልግሎት ጋር የተቀናጀ እንዲሆን አድርገናል። በዚሁም መሰረት ደንበኞች ስለክፍያ ሳይጨነቁ ጉዟቸውን ማቀድ የሚጀምሩበትን ‘Fly Now Pay Later’ ተብሎ የተሰየመውን የክፍያ አማራጭ ተግባራዊ ማድረጋችንን ስንገልጽ በደስታ ነው። ይህ የድህረ-ጉዞ ክፍያ አማራጭ ፕሮጀክት ዕውን እንዲሆን ከአየር መንገዳችን እና ከዳሽን ባንክ በኩል ለተሳተፉ አካላት ያለኝን ምስጋና በዚሁ አጋጣሚ ለመግለጽ እፈልጋለሁ።”

አዲሱን አገልግሎት ለመጠቀም አንድ ደንበኛ አስፈላጊ ቅድመ-ሁኔታዎችን ካሟላ በኋላ በቅርንጫፉ የተፈቀደለትን የብድር መጠን የሚወስድ ሲሆን የተፈቀደለትን ገንዘብ ለመጠቀም የሚያስችል የአንድ ጊዜ መለያ ቁጥር መልዕክትም በተንቀሳቃሽ ስልኩ የሚደርሰው ይሆናል። በመቀጠልም ደንበኛው የተሰጠውን መለያ ቁጥር በአየር መንገዱ የሞባይል መተግበሪያ ላይ በማስገባት ትኬት መቁረጥና የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን ይችላል።

ደንበኞች የተፈቀደላቸው የብድር መጠን ሲያልቅ ማደስ የሚችሉ ሲሆን በአንዴ የወሰዱትን ብድርም ለተለያዩ በረራዎች ከፍለው መጠቀም ይችላሉ።

አገልግሎቱ በተለይም በንግድ ስራ ላይ ለተሰማሩ፣ ጅምላ አስመጪዎች እና ለዕረፍት ከቤተሰቦቻቸው ጋር ወደ ውጭ ለሚሄዱ ደንበኞች አመቺ ነው።

በሁለቱ ተቋማት ስምምነት በቀረበው በዚህ አገልግሎት ተጠቃሚ ለመሆን የሚፈቀደው የብድር ገንዘብ መጠን እስከ ስድስት መቶ ሺህ (600,000) ብር የሚደርስ ነው።

የሚፈቀደው ብድር ወለድ የሚታሰብበት ሲሆን ይህም ደንበኛው በመረጠውና ብድሩን በወሰደበት የጊዜ ገደብ ከብድሩ ጋር አብሮ የሚከፈል ነው።

ብሔራዊ አየር መንገዱ እና ዳሽን ባንክ ወደፊትም የደንበኞችን አገልግሎት ለማዘመን አዳዲስ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በመጠቀም በትብብር መስራታቸውን ይቀጥላሉ።

Ethiopian, Dashen Bank Launch ’Fly Now Pay Later’ Service Package

Ethiopian, Dashen Bank Launch ’Fly Now Pay Later’ Service Package

Ethiopian, Dashen Bank Launch ’Fly Now Pay Later’ Service Package

  • The service allows passengers to fly without paying upfront
  • Ethiopian integrated the new Dashen Credit service to its Mobile app

December 28, 2023, Addis Ababa

Dashen Bank and the Ethiopian Airlines Group have jointly launched an innovative service package dubbed ‘Fly Now Pay Later’. This new technological innovation offers unprecedented flexibility and convenience for travelers allowing them to experience the unique opportunity to fly first and make payment at a later date. This pioneering move will redefine the travel experience.

The impact of technology in the travel industry is not only limited to registering business growth and profitability, but more importantly, it enhances the travel experience by reducing unnecessary steps that have traditionally contributed to travel ordeals.

Expressing his delight about the newly introduced service, Mr. Yohannes Million, Chief Digital Banking Officer of Dashen Bank said, “Fly Now Pay Later (FNPL) is an innovative way to purchase flights that allows travellers to book their trips without paying the full price upfront. The service will be available based on the customers’ choice of a 12- or 6-month payment period. Additionally, customers must open a bank account at Dashen Bank and remain as customers for at least three months in order to enjoy this service.”

Mr. Yohannes also emphasized that when customers go to the nearby Dashen Bank branch to apply, they are expected to present the necessary documents along with a guarantee.

Lauding the fruitful joint effort by the Ethiopian and Dashen team, Mr. Lemma Yadecha, Group Chief Commercial Officer of Ethiopian Airlines, said, “At Ethiopian, we place great value on system and technology modernization. System is one of our strategic growth pillars, and we continue to invest heavily in introducing cutting-edge technologies as part of our customer-centric endeavors. The new payment service we are launching today, ‘Fly Now, Pay Later,‘ will offer customers additional payment flexibility and enhance the customer experience. We have integrated our mobile app with the new payment strategy provided by Dashen Bank. We will further strive to make our system compatible with the best practices of other domestic banks as well.”

The credit period for this service is set for six to twelve months, and the credit limit can be renewed at the end of the credit tenure. Dashen Bank’s IT department has developed a desktop application that is integrated with the Ethiopian Airlines’ FlyGate application. Ethiopian Airlines, through its booking system, will provide confirmed passenger flight bookings and services upon successful payment confirmation received from Dashen Bank through FlyGate.

To use this service, customers will receive a spending limit from the Dashen Bank branch and an SMS confirmation that should be entered into Ethiopian Mobile app to purchase flight tickets. Passenger flight tickets can be purchased once or multiple times, up to the facility limit.

The credit limit is determined based on the customers’ borrowing capacity, up to a maximum of 600 thousand birr. The Fly Now Pay Later payment strategy has increasingly gained popularity in the travel industry.

5% ተመላሽ ገንዘብ ያግኙ!

5% ተመላሽ ገንዘብ ያግኙ!

5% ተመላሽ ገንዘብ ያግኙ!

ከታህሳስ 15 እስከ ጥር 14 ቀን፣ 2016 ዓ.ም ድረስ ግብይትዎን ከተቻ በተጠቀሱት ቦታዎች በዳሸን ባንክ ካርድ እና በአሞሌ ሲፈፅሙ የ5% ተመላሽ ገንዘብ ያግኛሉ፡፡ የሌሎች ባንኮች ካርዶችን በመጠቀም ከ10,000 ብር በላይ በዳሸን ፖስ ማሸን በመጠቀም ግብይትዎን ሲፈፅሙ የ500 ብር የስጦታ ካርድ ያገኛሉ፡፡

S.N Merchant
1 Queens Supermarket ኩዊንስ ሱፐርማርኬት
2 Fresh corner ፍሬሽ ኮርነር (Luna Export)
3 Shoa Supermarket ሸዋ ሱፐርማርኬት
4 Allmart supermarket ኦልማርት ሱፐርማርኬት
5 East Africa Trading House (Besh) በሽ ገበያ
6 Lewis Retails ሌዊስ ሪቴልስ (ባምቢስ ሱፐርማርኬት)
7 Lomyad Supermarket ሎምያድ ሱፐርማርኬት
8 Fanut and Family ፋንቱ ሱፐርማርኬት
9 Frendship Sup ፍሬንድሺፕ ሱፐርማርኬት
10 Boston Day spa ቦስተን ደይ ስፓ
11 Kuriftu Water park ኩሪፍቱ ወተር ፓርክ
12 Entoto Water park እንጦጦ ፓርክ
13 Purpose Black Ethiopia ከገበሬው ሱፐርማርኬት
14 Safeway Supermarket ሴፍዌይ ሱፐርማርኬት
15 Organic Meat Export ኦርጋኒከ ማርት
16 Abadir Shopping አባድር ሱፐርማርኬት
17 Lime Tree Restaurant ላይምትሪ ሬስቶራንት
18 Skylight Hotel ስካይ ላይት ሆቴል
19 Shoa Shoping center ሽዋ ሾፒንግ ሴንተር
20 Seven Eleven Supermarket ሰቨን ኢለቨን  ሱፐርማርኬት
21 F & W supermarket F & W ሱፐርማርኬት
22 Ambasader Garment ( 4 kilo)  አምባሳደር ልብስ ስፌት   4ኪሎ
23 Haile & Alem International Plc ኃይሌ እና አለም  ሆቴል – አዳማ
24 Ayu International Hotel አዩ ኢንተርናሽናል ሆቴል
25 Naflet Hotel ናፍሌት ሆቴል
26 Star Supermarket ስታር ሱፐርማርኬት
27 Robi Hotel ሮቢ ሆቴል
28 Bekele Mola Hotel ( Hibr Restaurant) በቀለ ሞላ ሆቴል
29 Kidanmhiret Hotel ኪዳነማሪያም ሆቴል
30 Rift Valley Hotel ሪፍትቫሊ ሆቴል
31 Canopy Hotel ካኖፒ ሆቴል
32 Daka Hotel ዳካ ሆቴል
33 Yaden Hotel ያደን ሆቴል
34 Kelole Hotel ኬሎሌ ሆቴል
35 Lisak Resort & Spa ሊሳቅ ሪዞርት እና ስፓ
36 Asham Africa Hotel And Resort አሻም አፍሪካ ሆቴል እና ሪዞርት
37 Piramid Hotel & Resort ፒራሚድ ሆቴል እና ሪዞርት
38 Tk International Hotel And Resort ቲኬ ኢንተርናሽናል ሆቴል እና ሪዞርት
39 Bezi Supermarket ቤዚ ሱፐርማርኬት
40 Atinaf Bouchery አጥናፉ ስጋቤት
41 DIANA III PASTACALDI  
42 Arirang Restourant አሪራንግ ሬስቶራንት
43 Dr.Kalid & His Family ዶክተር ካሊድ እና ቤተሰቦቹ
44 Al-Afia Hospital አል አፍያ ሆሰፒታል
45 Tezenea General Hospital ተዘንኣ ጠቅላላ ሆስፒታል
46 Odoni Hotel ኦዶኒ ሆቴል
47 Tirar International Hotel ጥራር ኢንተርናሽናል ሆቴል
48 Churchill Hotel ቸርችል ሆቴል
49 Trinity Hotel ትሪኒቲ ሆቴል
50 Brostamifa Trading & Hospitality Service Plc  

Facebook
Twitter
YouTube
LinkedIn
Instagram
Telegram