Select Page
የዳሸን ባንክ 28ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እና የሠራተኞች ቀን

የዳሸን ባንክ 28ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እና የሠራተኞች ቀን

የዳሸን ባንክ 28ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እና የሠራተኞች ቀን

Donation to Somali Regional State

Donation to Somali Regional State

Donation to Somali Regional State

Dashen American Express International card Inaguration

Dashen American Express International card Inaguration

Dashen American Express International card Inaguration

28th Ordinary & 25th Extra Ordinary Annual Shareholder Meeting at Mechare Meda

28th Ordinary & 25th Extra Ordinary Annual Shareholder Meeting at Mechare Meda

28th Ordinary & 25th Extra Ordinary Annual Shareholder Meeting at Mechare Meda

The 27th Ordinary and 24th Extra Ordinary General Meeting of Shareholders of Dashen Bank

The 27th Ordinary and 24th Extra Ordinary General Meeting of Shareholders of Dashen Bank

The 27th Ordinary and 24th Extra Ordinary General Meeting of Shareholders of Dashen Bank

ዳሽን ባንክ የ 10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ለኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝ መከላከያ ዝግጅት አበረከተ

ዳሽን ባንክ የ 10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ለኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝ መከላከያ ዝግጅት አበረከተ

ዳሽን ባንክ የ 10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ለኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝ መከላከያ ዝግጅት አበረከተ

(አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22 ቀን 2012 ዓ.ም) ዳሽን ባንክ ለኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝ መከላከል ዝግጅት የሚውል ገንዘብ እና ሌሎች አቅርቦቶችን ለማሰባሰብ የቀረበውን አገራዊ ጥሪ ተከትሎ ፤ በመንግሥት ለተቋቋመዉ ብሔራዊ የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ የብር 10,000,000.00 (አስር ሚሊዮን ብር) ድጋፍ ለገሰ ።

በቅርቡ “ የኅብረተሰብ ጤና የአገር ደኅንነትና ዕድገት መሠረት ነው ” በሚል መሪ ቃል ባንኩ የወስዳቸውን የማኅበራዊ ኃላፊነትን የመወጣት ግዴታዎች ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ነው ፡፡ ይህም  ደንበኞችን ከአካላዊ ንክኪ ርቀዉ የባንክ አገልግሎት እንዲያገኙ ከሚያስችሉ ዕርምጃዎች መካከል ኤ.ቲ.ኤም. ማሽኖችን ተጠቅመው ክፍያ በሚፈጽሙ ደንበኞች ላይ ይተገበር የነበረውን የኮሚሽን ክፍያ ሙሉ በሙሉ በማንሳት በነፃ ክፍያ እንዲያከናወኑ ፣ ምርቶችን ከውጭ የሚያስገቡ ደንበኞች የሚያጋጥማቸውን የንግድ እንቅስቃሴ መስተጓጎል ከግምት ውስጥ በማስገባት ፤ ከዚህ በፊት ለባንክ መተማመኛ ሰነድ ብድር ወይም ለኤል.ሲ. ማራዘሚያ ይከፍሉ የነበረው ኮሚሽን ተነስቶ ነፃ እንዲሆን ፣  በቀጥታ የግዢ ትዕዛዝ ሰነድ ከውጭ ምርት ለሚያስገቡ ደንበኞች ለጊዜ ማራዘሚያ ይከፈሉ የነበረው ኮሚሽን በ 50 በመቶ እንዲቀንስ  ፣ የተበዳሪ ደንበኞች የንግድ እንቅስቃሴ ወረርሽኙ በሚፈጥረው ተፅዕኖ ምክንያት እንደሚቀዛቀዝ በመገመት ፤ የተመላሽ ብድሮች የመክፈያ ጊዜ እንዲራዘምላቸው ደንበኞች ጥያቄ በሚያቀርቡበት ወቅት ይከፍሉ የነበረው ኮሚሽን ተነስቶ በነፃ እንዲስተናገዱ ፣ ደንበኞች ወደ ባንኩ ቅርንጫፍ ሳይሔዱ የቪዛና የወለድ አልባ አገልግሎት የክፍያ ካርዶቻቸዉን በኤ.ቲ.ኤም. ማሽኖች ሲጠቀሙ  በየቀኑ የሚያወጡት ገንዘብ ላይ እጥረት እንዳያጋጥማቸዉ የዕለት ብር ወጪ መጠን ገደቡ ላይ ማሻሻያ በማድረግ ወደ አሥር ሺሕ ብር ከፍ እንዲል ሲያደርግ ፤ ባንኩ ወደ ፊትም  የወቅቱን ሁኔታ እያገናዘበ ተመሳሳይ እርምጃወችን እንደሚወስድ ማስታወቁ የሚታወስ ነው ፡፡

በዚሁም መሠረት ከላይ ከተጠቀሱት ከፍተኛ ዉሳኔዎች በተጨማሪ ዳሸን ባንክ ወረርሽኙ በህዝባችን ላይ የሚያሳድረውን የጤናና የኢኮኖሚ ተጽዕኖዎች በመገምግም ፤ ደንበኞቹንና ዜጎቻችንን የሚደግፍ ተመሳሳይ እርምጃዎችን እንደሚውስድ የገባውን ቃል በመጠበቅ ፤ የዳሽን ባንክ ዳይሬክተሮች ቦርድ የወሰነዉን የአሥር ሚሊዮን ብር ድጋፍ የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ዓለሙ ለብሔራዊ የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴው የኃብት ማሰባሰብ ኮሚቴ ሰብሳቢ አምባሳደር ምስጋኑ አረጋ አስረክበዋል ።

ዳሸን ባንክ ሁልጊዜም አንድ እርምጃ ቀዳሚ!

Facebook
Twitter
YouTube
LinkedIn
Instagram
Telegram