Select Page
በዳሸን ባንክ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አስፋው ዓለሙ የተመራ የባንኩ ከፍተኛ የሥራ አመራር አባላት የደንበኞች ሳምንትን በማስመልከት በዛሬው እለት በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በመገኘት ተቋሙ ከባንኩ ጋር ላለው ጠንካራ የስራ ግንኙነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በዳሸን ባንክ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አስፋው ዓለሙ የተመራ የባንኩ ከፍተኛ የሥራ አመራር አባላት የደንበኞች ሳምንትን በማስመልከት በዛሬው እለት በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በመገኘት ተቋሙ ከባንኩ ጋር ላለው ጠንካራ የስራ ግንኙነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በዳሸን ባንክ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አስፋው ዓለሙ የተመራ የባንኩ ከፍተኛ የሥራ አመራር አባላት የደንበኞች ሳምንትን በማስመልከት በዛሬው እለት በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በመገኘት ተቋሙ ከባንኩ ጋር ላለው ጠንካራ የስራ ግንኙነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በዳሸን ባንክ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አስፋው ዓለሙ የተመራ የባንኩ ከፍተኛ የሥራ አመራር አባላት የደንበኞች ሳምንትን በማስመልከት በትላንትናው እለት በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በመገኘት ተቋሙ ከባንኩ ጋር ላለው ጠንካራ የስራ ግንኙነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል አሕመድ ለባንኩ የሥራ አመራር አባላት አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ባሳለፍነው ሰኞ መከበር የጀመረው የዳሸን ባንክ የደንበኞች ሳምንት እሰከ መጪው ቅዳሜ በተለያዩ ዝግጅቶች ይቀጥላል።

 

 
(more…)

ዳሸን ባንክ ዓመታዊ የደንበኞች ሣምንትን እያከበረ ይገኛል

ዳሸን ባንክ ዓመታዊ የደንበኞች ሣምንትን እያከበረ ይገኛል

ዳሸን ባንክ ዓመታዊ የደንበኞች ሣምንትን እያከበረ ይገኛል

ዳሸን ባንክ ዓመታዊ የደንበኞች ሳምንትን በተለያዩ መርሃ-ግብሮች እያከበረ ይገኛል፡፡

የባንኩ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አስፋው ዓለሙ የደንበኞች ሣምንት ደንበኞች ከባንኩ ጋር ላላቸው አጋርነት ክብርና እውቅና ለመስጠት ያለመ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

የደንበኞች ሣምንት፤ደንበኞች የባንኩ ሕልውና እና መሠረት መሆናቸውን ለመመስከርና ደንበኛን ማዕከል ያደረገ አገልግሎት የመስጠት ዕሴታችንን አጉልተን ለማሣየት የምናከብረው ነው ብለዋል፡፡

ባንኩ ከአፍሪካ ምርጥ ባንኮች ውስጥ አንዱ ሆኖ የመገኘት ራዕዩን ለማሳካት የሚችለው በላቀ የደንበኞች አገልግሎት እንደሆነ የጠቆሙት አቶ አስፋው የባንኩን የስኬት ጉዞ ለማረጋገጥ ጊዜው የሚጠይቀውን የሙያ ብቃትና ተነሳሽነት አስቀጥሎ እንደሚጓዝም አብራርተዋል፡፡

አሁን ላይ ባለው ተለዋዋጭ ዓለም በባንክ ኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚስተዋለው ውድድር ውስብስብና ጠንካራ እንደሆነ ያነሱት ዋና ስራ አስፈጻሚው እያንዳንዱን ቀን በትጋትና በቁርጠኛነት በመስራት ገበያው የሚፈጥራቸውን ተግዳሮቶች ወደ ዕድል መለወጥ እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል፡፡

ዓመታዊ የደንበኞች ሣምንት እየተከበረባቸው ከሚገኙ የባንኩ ቅርንጫፎች መካከል አንዱ የሆነው አሙዲ ቅርንጫፍ ሲገለገሉ ያገኘናቸው ደንበኞች በበኩላቸው ዳሸን ባንክ ደንበኛን ያከበረ መስተንግዶ እየሰጠ እንደሆነ ተናረዋል፡፡

ባንኩ ከጊዜ ወደ ጊዜ አገልግሎቱን በማሻሻል አመርቂ ስራ እያከናወነ እንደሆነ የሚገልጹት ተገልጋዮች ደንበኞች በአካል ቀርበው ከሚያገኙት አገልግሎት ባሻገር በዲጅታል ባንኪንግ ዘርፍ አዳዲስ አማራጮችን እያቀረበ እንደሆነም ጠቅሰዋል፡፡

 

(more…)

ዳሸን ባንክ ለሐጅ ተጓዦች የተቀላጠፈ የባንክ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል

ዳሸን ባንክ ለሐጅ ተጓዦች የተቀላጠፈ የባንክ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል

ዳሸን ባንክ ለሐጅ ተጓዦች የተቀላጠፈ የባንክ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል

ዳሸን ባንክ ለሐጅ ተጓዦች የተቀላጠፈ የባንክ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል

ባንኩ በዘንድሮው ዓመት የሐጅ ስነ-ስርዓት ለመፈጸም ወደ ሳውዲ ዓረቢያ የሚጓዙ ሁጃጆችን  ባሉት ቅርንጫፎች አገልግሎት እየሰጠ ነው፡፡

ዳሸን ባንክ ለሐጅ ተጓዦች ከ80 በላይ ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ አገልግሎት በሚሰጡ ቅርንጫፎችና ከ800 በላይ በተዘጋጁ መስኮቶች የተቀላጠፈ የባንክ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።

የሐጅ ሐይማኖታዊ ስነ-ስርዓትን ለመፈጸም የሚጓዙ ምዕመናን ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች የተሰጣቸውን የተመዘገቡበትን መለያ ኮድ ይዘው በመምጣት በባንኩ ሁሉም ቅርንጫፎች ክፍያቸውን በቀላሉ መፈጸም ይችላሉ፡፡

ተጓዥ ምዕመናን በዳሸን ባንክ በኩል ክፍያቸውን ሲፈጽሙ በውጭ ሐገር ቆይታቸው የሚጠቀሙበትን የውጭ ምንዛሬ ያመቻቻል፡፡ ባንኩ ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ጋር በጋራ እየሰራ ሲሆን ም/ቤቱ በመላው ሐገሪቱ ለሐጅ ምዝገባ ባዘጋጃቸው 30 ማዕከላት ተጓዦችን እያስተናገደ ይገኛል፡፡

የሐጅ ተጓዦች ከጥር 15 ቀን 2017 ጀምሮ ባሉበት አካባቢ መመዝገብ የሚችሉ ሲሆን ክፍያቸውን እንግልት ሳይገጥማቸው በዳሸን ባንክ ቅርንጫፎች በኩል በቀላሉ መፈጸም ይችላሉ፡፡ ምክር ቤቱ የሐጅ ተጓዦችን በፍጥነት በመመዝገብ ጊዜያቸውን እንዲቆጥቡና የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲያገኙም ጥሪ አቅርቧል፡፡

 

(more…)

ዳሸን ባንክ በፕላቲኒየም ደረጃ ስፖንሰር ያደረገው ኤግዚቢሽን ተከፈተ

ዳሸን ባንክ በፕላቲኒየም ደረጃ ስፖንሰር ያደረገው ኤግዚቢሽን ተከፈተ

ዳሸን ባንክ በፕላቲኒየም ደረጃ ስፖንሰር ያደረገው ኤግዚቢሽን ተከፈተ

ዳሸን ባንክ ዋና አጋር የሆነበት የዲያስፖራ አውደ-ርዕይ በዛሬው ዕለት በግዮን ሆቴል በይፋ ተከፍቷል።

አውደ-ርዕዩ  የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማኀበር ከሮሆቦት ፕሮሞሽን ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ነው ።

በዳሸን ባንክ ዲያስፓራ ባንኪንግ መምሪያ ከፍተኛ ስራ አስኪያጅ  አቶ ካሱ ጌታቸው በአውደ-ርዕዩ ላይ ባንኩ በቅርቡ ይፋ የሆነውን ዳሸን ሱፐር አፕን ጨምሮ ሌሎች አገልግሎቶችን እያስተዋወቀ እንደሆነ ገልጸዋል።

ባንኩ ለዲያስፓራው ምቹ የሆኑና የተለያዩ አማራጮች ያሏቸውን የዲያስፓራ ተንቀሳቃሽ ሒሳብ፣በውጭ ሀገር ገንዘብ የሚከፈት የቁጠባ ሂሳብ፣ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎትና ሌሎች ለዲያስፖራው ማህበረሰብ ምቹ አገልግሎቶችን እየሰጠ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

አውደ-ርዕዩን ያስጀመሩት የኢትዮጵያ ዲያስፓራ አገልግሎት ተወካይ አምባሳደር አንተነህ ታሪኩ የዲያስፖራው ማህበረሰብ ለበዓላት ወደ ሀገር ቤት የገቡ እንደመሆናቸው የኢንቨስትመንት አማራጮችን እንዲመለከቱ ጋብዘዋል።

ማኀበሩ ከኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎትና ሌሎች ተቋማት ጋር በትብብር እየሰራ እንደሆነም ተናግረዋል።

ዲያስፖራው ማህበረሰብ የሀገር ቤት ቆይታውን ቀላል የሚያደርጉለት የተለያዩ የባንክ አገልግሎቶችን መጠቀም እንደሚችልም አመላክተዋል።

ዛሬ የተጀመረው የዲያስፖራ ሳምንት በትብብር ለሀገር ለመስራት የምንመክርበት ነው ብለዋል። አውደ-ርዕዩ በቀጣይ በካናዳ ቶሮንቶ እንደሚካሄድም ተጠቁሟል።  ኤግዚቢሽኑ እስከ ነገ ድረስ እንደሚቀጥል የተመላከተ ሲሆን የሀገር ውስጥ ምርትና አገልግሎቶች ይተዋወቁበታል።

      

(more…)

Dashen Bank Unveils the first Banking Super App – Redefining Digital Banking

Dashen Bank Unveils the first Banking Super App – Redefining Digital Banking

Dashen Bank Unveils the first Banking Super App – Redefining Digital Banking

Press Release

 

(Addis Ababa, January 14, 2025)- Dashen Bank has launched a banking Super App, the first of its kind in Ethiopia’s banking industry and a cutting-edge, all-in-one banking solution  at the Sheraton Addis Hotel. This new platform offers a wide range of features, designed for speed, reliability, and customer satisfaction.

“As Dashen Bank, we are excited to launch the Dashen Bank Super App, which will empower us to achieve our vision of being truly customer-centric,” said Asfaw Alemu, CEO of Dashen Bank, during the grand launching ceremony. This app will enable us to provide safer, higher-quality, and more efficient digital services for businesses at every level.”

 

 He also added, “With the Dashen Bank Super App, we are taking our digital banking services ‘one step ahead,’ as our motto proudly asserts. We remain committed to delivering innovative, up-to-date, and reliable digital banking solutions in collaboration with strategic partners.”

The Dashen Super App sets a new benchmark for digital banking. With its sleek interface and robust functionality, the app seamlessly integrates every aspect of personal and business banking into one intuitive platform.

All-in-One Banking: Dashen Super App allows comprehensive features like accessing multiple accounts, transfer funds within and between banks instantly, access credit services based on transaction history, and manage finances—all in one place.

AI-Powered Seamless Onboarding: The Dashen Super App features an AI-powered self-onboarding process that verifies customer identity and performs a liveness check to bridge a gap in the Bank’s customer data, ensuring accurate and up-to-date information.

Empowering Every User

Interest Free Banking: The new Super App offers customers with not only conventional banking services but also a range of Sharia-compliant interest-free banking options.

Budget Management: The Super App also introduces an innovative “Budget” feature, empowering customers to take control of their finances. By tracking their spending across different categories, customers can gain valuable insights into their financial habits and make informed decisions.

Merchant App: Another new service offered by the Super App is “Three Click Shopping,” which allows customers to quickly and easily purchase various products and services with just three clicks. The Dashen Bank Super App enables businesses to sell their products on the app, in the same way from global marketplaces like Amazon and Alibaba. The Super App allows customers to make seamless purchases directly from their accounts. It also provides a convenient option for customers to get virtual cards, eliminating the need for physical cards and offering enhanced security. With the Super App, customers can easily make payments and transfer money using convenient QR code technology.

By integrating numerous applications, the Super App offers a comprehensive suite of services, enabling customers to conduct various transactions and access multiple features within a single platform. The Super App incorporates a diverse range of third-party applications, enabling users to book flights, access entertainment services such as local movie streaming and DStv subscriptions, and utilize a multitude of other services within the platform.

The Super App also features an innovative service called “Chat Banking,” which is offered for the first time in Ethiopian banking industry. This service allows customers to quickly transfer money using text messages through various social media platforms. To utilize this service, both the sender and the recipient must have an account on the Dashan Super App.

The Dashen Super App will introduce a phased approach, with the second phase offering customers the ability to access micro loans directly through the app, based on their transaction history.

Moreover, a savings feature, enabling customers to allocate a portion of their deposits to a designated savings account with a competitive interest rate will also be introduced.

As a pioneer in introducing various innovative banking technologies, Dashen Bank has once again set a new standard with the launch of its Super App. This App introduces numerous new services to the banking industry, enabling the bank to provide more modern and efficient services.

A Bold Vision for the Future

The Dashen Super App will be available for download on iOS and Android, bringing the future of banking to your fingertips.

      

(more…)

ዳሸን ባንክ በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ የመጀመሪያውን ሱፐር አፕ ለአገልግሎት አቀረበ

ዳሸን ባንክ በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ የመጀመሪያውን ሱፐር አፕ ለአገልግሎት አቀረበ

ዳሸን ባንክ በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ የመጀመሪያውን ሱፐር አፕ ለአገልግሎት አቀረበ

ጋዜጣዊ መግለጫ
 
(አዲስ አበባ: ጥር 06: 2017 ዓ.ም)- ዳሸን ባንክ በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የመጀመሪያ የሆነውንና በርካታ አገልግሎቶችን በአንድ ማዕቀፍ ያካተተ ዘመናዊ፣ ፈጣንና አስተማማኝ አገልግሎት ማቅረብ የሚያስችል ሱፐር አፕ (መተግበሪያ) በሸራተን አዲስ ሆቴል አስመርቋል፡፡
 
የዳሸን ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ዓለሙ ባደረጉት ንግግር ‘’ዳሸን ባንክ ሱፐር አፕ የበለጠ አቅም ይፈጥርልናል፡፡ በሁሉም የስራ ዘርፎች ለተሰማሩ ደንበኞቻችን ይበልጥ አሰተማማኝ፣ ጥራት ያለውና ውጤታማ አገልግሎት በመስጠት ደንበኛ-ተኮር አገልግሎት ለመስጠት ያስቀመጥነውን ራዕይ ይበልጥ ዕውን ለማድረግ ያስችለናል” ብለዋል፡፡ ዳሸን ባንክ ሱፐር አፕ የባንኩን ዲጂታል የባንክ አገልግሎቶች አንድ እርምጃ ወደፊት የሚወስድ መሆኑንም አስገንዝበዋል፡፡
 
አቶ አስፋው ዳሸን ባንክ ከዋና ዋና አጋሮች ጋር በመተባበር አዳዲስ፣ ዘመናዊ እና አስተማማኝ የዲጂታል ባንክ አገልግሎቶችን ማቅረቡን ይበልጥ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አመልክተዋል፡፡
 
ዳሸን ባንክ ሱፐርአፕ በዲጂታል ባንኪንግ ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ መተግበሪያ ነው፡፡ ለአጠቃቀም ምቹና ለእይታም ማራኪ የሆነው መተግበሪው በግል ሂሳብ እና ለተለያዩ የቢዝነስ ተቋማት አገልግሎት መስጠት እንዲያስችል ሆኖ የቀረበ ነው፡፡
 
ሁሉን በአንድ ያቀፈ የባንክ አገልግሎት፡ ይህ ሱፐር አፕ በርካታ አገልግሎቶችን ያካተተ ሲሆን አካውንቶችን መክፈት፣ ከአካውንት ወደ አካውንት በፍጥነት ገንዘብ ማስተላለፍ፣ እንዲሁም በገንዘብ ልውውጥ ላይ የተመሰረተ የብድር አገልግሎት መስጠትና ሌሎች አገልግሎቶችን በአንድ የያዘ መተግበሪያ ነው፡፡
 
ትክክለኛ የደንበኞች መረጃ፡ ይህ ሱፐር አፕ የደንበኞችን ማንነትና በህይወት መኖራቸውን ለማረጋገጥ የሚያስችል በመሆኑ ከዚህ ጋር ተያይዞ የነበረውን ክፍተት በማስቀረት ባንኩ የተረጋገጠ የደንበኞች መረጃ እንዲኖረው ያስችላል፡፡
ለሁሉም ደንበኛ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል፡
 
ደንበኞች በአዲሱ ሱፐር አፕ ከመደበኛ የባንክ አገልግሎት በተጨማሪ በሸሪዓህ ህግ መሰረት የቀረቡ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎቶችን ማግኘት ይችላሉ፡፡
 
ሌላው በዚህ ሱፐር አፕ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚቀርበው አገልግሎት ደንበኞች የግል ወጪያቸውን መምራት የሚችሉበት “በጀት” የተሰኘ አገልግሎት ነው፡፡ ይህ አገልግሎት ደንበኞች ለተለያዩ ዕለታዊ፣ ወርሃዊና አመታዊ ወጪዎቻው የመደቡትን የተለያየ በጀት በመከታተል ያለበትን ደረጃ ስለሚያሳውቅ የፋይናንስ አጠቃቀማችንን በአግባቡ ለመምራት ያግዛል፡፡
 
ዳሸን ሱፐር አፕ ካካተታቸው አዲስ አገልግሎቶች ሌላኛው ደንበኞች በሶስት ንክኪ ብቻ (Three Click Shopping) የተለያዩ ምርቶችና አገልግሎቶችን በፍጥነትና አመቺ በሆነ መልኩ መገብየት የሚያስችለው ነው፡፡ ዳሸን ባንክ ሱፐር አፕ በሌላው አለም እንደሚታወቁት አማዞንና አሊባባ ነጋዴዎች ምርታቸውን በሱፐር አፑ በማቅረብ መሸጥ የሚችሉበት ዕድል ይፈጥራል፡፡ የዚህ ግብይት ተጠቃሚዎች ክፍያቸውን በዳሸን ሱፐር አፕ አካውንታቸው በኩል በቀላሉ በመፈፀም መገበያየት ይችላሉ፡፡
 
ይህ ሱፐር አፕ ደንበኞች ዲጂታል ካርድ ወይም ቨርቹዋል ካርድ በማውጣት ከፕላስቲክ ካርዶች የተሻለ ፈጣንና አስተማማኝ አገልግሎት እንዲያገኙም አማራጭ አቅርቧል፡፡ ዳሸን ባንክ ሱፐር አፕ ደንበኞች በፍጥነት በኪው አር ኮድ አማካኝነት ክፍያ እንዲፈጽሙ እና ገንዘብ እንዲለዋወጡ የሚያስችል ነው፡፡
 
ዳሸን ባንክ ሱፐር አፕ በውስጡ በርካታ የተለያዩ አገልግሎቶችን መስጠት የሚችሉ መተግበሪያዎች ያካተተ በመሆኑ ደንበኞች ሌላ የአገልግሎት አማራጮችን መክፈት ሳያስፈልጋቸው በዚህ ሱፕር አፕ በርካታ አገልግሎቶችን በፍጥነት ማግኘት ይችላሉ፡፡ ለምሳሌ የአየር ትኬት ለመቁረጥና ተያያዥ አገልግሎቶችን ለማግኘት፣ በቴሌቲቪ አማካኝነት የአገር ውስጥ ፊልሞች ለመመልከት፣ የዲሴስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘትና ሌሎች በርካታ አገልግሎቶችን ማግኘት የሚያስችሉ መተግበሪያዎችን ያካተተ ነው፡፡
 
እስካሁን ያልነበረና ለአገራችን የባንክ አገልግሎት ዘርፍ የመጀመሪያ የሆነውና በዚህ ሱፐር አፕ የተካተተው አገልግሎት “ቻት ባንኪንግ” ይሰኛል፡፡ ይህ አገልግሎት ደንበኞች በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ በስልካቸው የፅሁፍ መልዕክት በመለዋወጥ ገንዘብ በፍጥነት መላላክ ያስችላል፡፡ ይህን አገልግሎት ለመጠቀም ሁለቱም ገንዘብ የሚላላኩ ደንበኞች የዳሸን ሱፐር አፕ ተጠቃሚ መሆን አለባቸው፡፡
 
በዳሸን ሱፐር አፕ የተካተቱ በርካታ አገልግሎቶች በቅደም ተከተል የሚቀርቡ ሲሆን በሁለተኛው ምዕራፍ ደንበኞች በሱፐር አፑ በሚያደርጉት አጠቃላይ የገንዘብ ልውውጥ ላይ የተመሰረት አነስተኛ የብድር አገልግሎት በቀጥታ ማግኘት ያስችላቸዋል፡፡
 
በዚሁ ምዕራፍ ደንበኞች ካላቸው ተቀማጭ ገንዘብ ቀንሰውና የሚቆጥቡበትን የጊዜ ገደብ ራሳቸው ወስነው ካዝና ውስጥ ተቀማጭ በማድረግ የወለድ ክፍያ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዕድል የሚሰጥ አገልግሎትም የሚጀምር ይሆናል፡፡
 
ዳሸን ባንክ የተለያዩ ፈር ቀዳጅ የባንክ ዘርፍ ቴክኖሎጂዎችን በተደጋጋሚ ያስተዋወቀ ሲሆን አሁን ለአገልግሎት ያበቃው ዳሸን ባንክ ሱፐት አፕ በርካታ አዳዲስ የአገልግሎት አማራጮችን ለባንክ ኢንዱስትሪው በማስተዋወቅ ባንኩ ይበልጥ ዘመናዊ አገልግሎት መስጠት የሚችልበት አማራጭ ይሆናል፡፡

 

 

      

(more…)

Facebook
Twitter
YouTube
LinkedIn
Instagram
Telegram