Select Page
ዳሸን ባንክ ለኢትዮጵያ ባንኮች የመጀመሪያ የሆነውን የ40 ሚሊየን ዶላር ብድር አገኘ

ዳሸን ባንክ ለኢትዮጵያ ባንኮች የመጀመሪያ የሆነውን የ40 ሚሊየን ዶላር ብድር አገኘ

ዳሸን ባንክ ለኢትዮጵያ ባንኮች የመጀመሪያ የሆነውን የ40 ሚሊየን ዶላር ብድር አገኘ

– ባንኩ ያገኘው ብድር ለወጪ ንግድ የሚሰጠውን ብድር ይበልጥ እንዲያጠናክር ያስችለዋል፡፡
– ለውጭ ምንዛሪ የሚሰጠው ብድር የግብርና ምርት ላኪዎች አዳዲስ ማሽነሪዎችን በመግዛት የምርት ሂደታቸውን እንዲያዘምኑና ምርታማነታቸውን እንዲያሳድጉ ያግዛል።
– የኢትዮጵያ የግብርና ምርት ላኪዎችን የገቢ አቅም በማሳደግ ምርታማነትን ያሳድጋል፡፡

(አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 23 ቀን 2023)- የእንግሊዝ ዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንት (ቢ አይ አይ) እና የኔዘርላንድ የስራ ፈጠራና ልማት ባንክ የሆነው ኤፍ ኤም ኦ እያንዳንዳቸው 20 ሚሊየን ዶላር በድምሩ 40 ሚሊየን ዶላር ብድር በኢትዮጵያ ቀዳሚ ከሆኑት ባንኮች አንዱ ለሆነው ለዳሸን ባንክ ማቅረባቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡ ይህ የብድር አቅርቦት ኢትዮጵያ ለውጪ ገበያ የምታቀርበውን የግብርና ምርት ለማሳደግ እና በእጅጉ አስፈላጊ የሆነውን የውጪ ምንዛሬ አቅርቦት ለማሻሻል ያስችላል፡፡

ቢ አይ አይ እና ኤፍኤምኦ ለዳሸን ባንክ ያቀረቡት ገንዘብ በኢትዮጵያ 80% የህብረተሰብ ክፍል በተሰማራበት፣ ለጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት 39 % ድርሻ ላለው እና ለወጪ ንግዱ 90 % አስተዋጽኦ ለሚያበረክተው የግብርና ዘርፍ ከፍተኛ እገዛ እንደሚኖረው ይታመናል፡፡

የቀረበው ብድር ባንኩ የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ለማሳደግ ለሚያደርገው ጥረት የበኩሉን እገዛ ያደርጋል፡፡ በተለይ በእርሻ ስራ ላይ ለተሰማሩ ምርታማነትን ለመጨመር የሚያስችሉ ግብአቶችን በማሟላት ከኤክስፖርት የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ አስተዋጽኦ ያበረክታል፡፡

ብድሩ በሀገሪቱ ከፍተኛ እጥረት በሚታይበት የውጭ ምንዛሪ በመቅረቡ ባንኩ ዓይነተ-ብዙ አገልግሎቶችን ለደንበኞቹ ለማቅረብ የሚያግዝ ይሆናል፡፡ ይህም በአመራረት፣ በማጓጓዝ እና በማቀናበር ሂደቶች ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ ዘመናዊ መሳሪያዎችን ከውጭ ለማስገባት የውጭ ምንዛሪ ማቅረብን ይጨምራል፡፡

የፋይናንስ ተቋማት ትብብር ለግሉ ዘርፍ እድገት ጉልህ ሚና አለው፡፡በዚህ ትብብር ቢአይአይ እና ኤፍኤምኦ. የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እ.ኤ.አ በ 2021 አዲስ ባወጣው የውጭ ማንዛሪ ማቀላጠፊያ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ለሚገኝ የፋይናንስ ተቋም በውጭ ምንዛሪ የቀረበ የረዥም ጊዜ ብድር ሲሰጡ የመጀመሪያዎቹ ናቸው፡፡ይህ ፋና ወጊ ተግባር ገበያውን በማነቃቃት ከዓለም አቀፍ መዋዕለ-ንዋይ አቅራቢዎች ተጨማሪ ሀብት ለማሰባሰብ መተማመንን ለመገንባት ያግዛል፡፡

በሚቀጥሉት አስር አመታት በአማካይ በ6.2 በመቶ እንዲያድግ ከሚጠበቀው የኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ አንጻር በቢአይአይ እና ኤፍኤምኦ የቀረበው ፋይናንስ ኢትዮጵያውያን ላኪዎች ተጨማሪ የውጭ ምንዛሪ እንዲያመነጩ ከእነሱ አልፎም ለላኪዎቹ ምርታቸውን የሚያቀርቡ አነስተኛ አምራቾች ምርታቸውን በቀጣይነት በማሳደግ ከውጭ ንግዱ ይበልጥ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያስችል ነው፡፡

በግብርና ለተሰማሩ የንግድ ተቋማት የሚቀርብ ፋይናንስ ከአበባ እስከ ቡና እና የቁም ከብት ድረስ የተሻሻሉ የአመራረት ዘዴዎችን ለማስተዋወቅ፣ ጥራትን ለማሳደግ፣ ዓለም አቀፍ ደረጃዎችን ለማሟላት እና እሴት ለመጨመር የጎላ ሚና ይኖረዋል፡፡ የፋይናንስ አቅርቦቱ በግብርና ወጪ ንግድ ዙሪያ የተሰማሩ አምራቾችና ነጋዴዎችን የኢኮኖሚ አቅም በማጎልበት ከ 45 በመቶ ያልበለጠ የማህበረሰብ ክፍል ብቻ የባንክ አካውንት ባለቤት በሆነባት ሀገራችን የፋይናንስ አካታችነትን ለማሳደግ አጋዥ ይሆናል፡፡

በዚህ ትብብር ቢአይአይ እና ኤፍኤምኦ ከዳሸን ባንክ ጋር በአመራር ስጋት አስተዳደር፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ በማህበራዊ እና ስርዓተ – ጾታ ዘርፎች ዙሪያ ዓለም አቀፍ ደረጃዎችን በኢትዮጵያ ለማስተዋወቅ እና ለማስረፅ በቅርበት ይሰራሉ፡፡

የዳሸን ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ዓለሙ እንደገለጹት ” ተምሳሌታዊ በሆነው ቢአይአይ እና ኤፍኤምኦ በትብብር የሰጡን ብድር የውጭ ምንዛሪ ማመንጨት የሚችሉ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ከውጭ የፋይናንስ ተቋማት በኢትዮጵያውያን ባንኮች በኩል ፋይናንስ ማግኘት የሚችሉበትን የብሄራዊ ባንክ መመሪያ ተግባራዊ በማድረግ ፋና ወጊ በመሆናችን ደስታችን የላቀ ነው፡፡ በውጭ ምንዛሪ የቀረበው ብድር በውጭ ንግድ ላይ የተሰማሩ ደንበኞችን ለማገዝ እንደሚውል እና ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በእጅጉ የሚያስፈልገውን የውጭ ምንዛሪ ባንካችን ከሁለቱ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ጋር በመስራቱ ለሀገር የሚተርፍ በርካታ ልምድ፣ እውቀትና የአሰራር ዘይቤ ተቀስሟል፡፡ ባንካችን ከሁለቱ የልማት አጋሮቹ ላገኘው ድጋፍ ከፍተኛ ምስጋና አለን ” ሲሉ ገልጸዋል፡፡

በመጨረሻም ሁለቱ ተቋማት በዳሸን ባንክ ውጤታማነትና በኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ ላይ ሙሉ እምነት በመጣል የፋይናንስ አቅርቦት በማድረጋቸው ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማቸውም ዋና ስራ አስፈጻሚው ተናግረዋል፡፡

የቢ አይ አይ ዋና ስራ አስፈጻሚና የፋይናንሺያል አገልግሎት ኃላፊ የሆኑት ስቴፈን ፕሪስትሊ በአለምአቀፍ ኢንቨስትመንት ላይ የመጀመሪያዎቹ ተቋማት በመሆናቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸው ቢ አይ አይ በኢትዮጵያ ከ50 አመታት በፊት ኢንቨስት ማድረጉንም አስታውቀዋል፡፡ ” በዚህ የፋይናንስ አቅርቦት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እየከፈተ ወዳለው ገበያ ቀድመን ለመግባት ከቀዳሚዎቹ ውስጥ በመሆናችን ኩራት ተሰምቶናል፡፡ባለፉት 50 ዓመታት ቢአይአይ በኢትዮጵያ ቀዳሚ መዋዕለ-ነዋይ አፍሳሽ ሆኖ ቆይቷል፡፡ ከኤፍኤምኦ ጋር የደረስንበት አጋርነት ወደ ኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ በልማት የፋይናንስ አቅራቢዎችና የንግድ መዋዕለ-ንዋይ አንቀሳቃሾች ትብብር ሊመጣ የሚችለውን ከፍ ያለ ሀብት አመላካች ነው፡፡ ” ሲሉ ገልጸዋል፡፡

የኤፍ ኤም ኦ የፋይናንሺያል ኢንስቲትዩሽን ዲፓርትመንት ዳይሬክተር ማርኒክስ ሞንስፎርት እንደተናገሩት” ዳሸን ባንክ እና ኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ መዋዕለ-ንዋይ እና የውጭ ምንዛሪ አቅርቦት እንዲያገኙ በሚያስችለው በዚህ ፈር ቀዳጅ አጋጣሚ በመሳተፋችን ደስተኞች ነን፡፡ በእጅጉ አስፈላጊ የሆነውን በውጭ ምንዛሪ ብድር በውጪ ንግድ ላይ ያተኮረ ግብርና በመደገፍ ለሥራ ፈጠራና በገጠር አካባቢ የፋይናንስ አካታችነትን በማስፈን አስተዋጽኦ ለማድረግ ህልማችን ነው፡፡ ለዚህ ታላቅ ትብብር ዳሸን ባንክን እና ቢአይአይን እናመሰግናለን፡፡ ” በማለት ገልጸዋል፡፡

 

 

 

(more…)

Dashen Bank and Mastercard join forces to launch the first virtual prepaid card in Ethiopia

Dashen Bank and Mastercard join forces to launch the first virtual prepaid card in Ethiopia

Dashen Bank and Mastercard join forces to launch the first virtual prepaid card in Ethiopia

  • The card offers both plastic and virtual capabilities allowing customers to choose their preferred payment method.
  • The new card will provide foreign payment options, simplifying international payments
  • The partnership will also drive sustainable growth and inclusion of small businesses in Ethiopia through the Mastercard Payment Gateway system that will make digital and e-commerce payments more seamless, smart, and swift

Addis Ababa, Ethiopia – 17 August 2023: Dashen Bank has partnered with Mastercard to introduce the ‘Dashen Mastercard’, a ground-breaking multi-currency international prepaid card. This announcement was made during a press conference held at the bank’s headquarters, marking a significant milestone in Ethiopia’s card business. The card offers both plastic and virtual options, providing customers with unparalleled flexibility and convenience for their international transactions.

The Dashen Mastercard features a dual-interface plastic card, allowing customers to make both contact or contactless transactions at ATMs and POS machines. It also enables cash withdrawals from ATMs, payments on POS terminals, and offers users the freedom to make online purchases at any merchant website worldwide where Mastercard is accepted.

A key feature of the Dashen Mastercard is its reloadable nature, allowing users to load funds onto the card as needed at forex bureaus. The card also supports multiple currencies, enabling customers to have separate wallet accounts in different currency types, thus eliminating the need for a separate foreign currency account. This feature makes it an ideal choice for international payments and travel-related expenses.

To ensure maximum security, the Dashen Mastercard incorporates an additional layer of protection by providing customers with a One-Time Password (OTP) for every transaction made on e-commerce platforms. This feature enhances customer confidence and safeguards against unauthorized use of the card.

“This innovative offering is a testament to Dashen Bank’s commitment to delivering convenient and secure financial solutions to our customers,” said Mr Asfaw Alemu, Chief Executive Officer at Dashen Bank. “The Dashen Mastercard empowers travelers with the freedom to manage their finances seamlessly while exploring the world.”

In addition to the card launch, Dashen Bank and Mastercard have also introduced the Mastercard Payment Gateway System, allowing Ethiopian merchants with mobile applications or websites to accept international payments online. Customers from around the world can now place online orders and reservations and make payments to merchants integrated with the Mastercard Payment Gateway System using their cards. This product aligns with Ethiopia’s digital transformation strategy by facilitating smooth cross-border payments.

“Our partnership with Dashen Bank marks a significant milestone in our efforts to join forces with financial institutions in Ethiopia by leveraging the power of our products and solutions to bring more people into the digital economy,” said Shehryar Ali, Country Manager for East Africa at Mastercard. ” We are proud to collaborate with Dashen Bank to enhance the drive to access financial services, and our shared commitment to grow innovative payment solutions and seamless transactions for merchants and customers alike.”

The Dashen Mastercard is available to travelers above the age of 18. Interested individuals can obtain the card by visiting any of Dashen Bank forex bureau or branch and providing essential travel documents such as a passport, visa, and flight ticket that are required during the application process.

 

 

(more…)

ዳሸን ባንክና ማስተርካርድ የመጀመሪያውን ቨርቹዋል አለም አቀፍ ቅድመ ክፍያ ካርድ አስተዋወቁ

ዳሸን ባንክና ማስተርካርድ የመጀመሪያውን ቨርቹዋል አለም አቀፍ ቅድመ ክፍያ ካርድ አስተዋወቁ

ዳሸን ባንክና ማስተርካርድ የመጀመሪያውን ቨርቹዋል አለም አቀፍ ቅድመ ክፍያ ካርድ አስተዋወቁ

አዲስ አበባነሃሴ 09-2015 . ዳሸን ባንክ አለም አቀፍ ቅድመ ክፍያ ካርድ ከማስተርካድ ጋር በመተባበር ከተለመደው በስም ከሚታተም የፕላስቲክ ካርድ በተጨማሪ በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ታሪክ የመጀመሪያ የሆነ ቨርቹዋል ካርድን በማምጣት  ዛሬ በሸራተን አዲስ ሆቴል አስተዋውቀዋል፡፡

የዳሸን ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ዓለሙ በስነ-ስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር ዳሸን ባንክ ይህን በአይነቱ የተለየ ካርድ ማስተዋወቁ ባንኩ ለደንበኞቹ ቀላል፣ ምቹና አስተማማኝ የፍይናንስ አገልግሎቶችን ይበልጥ ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል፡፡

ካርዱ ደንበኞች በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ገንዘባቸውን ያለምንም ስጋት መጠቀም የሚችሉበት አማራጭ መሆኑንም አመልክተዋል፡፡

የማስተርካርድ የምስራቅ አፍሪካ ስራ አስኪያጅ ሸህርያር አሊ በበኩላቸው ማስተርካርድ ከዳሸን ባንክ ጋር የፈጠረው ጥምረት በኢትዮጵያ እንደ አለም አቀም ካርድ ያሉ አገልግሎቶችን በማስተዋወቅ ማህበረሰቡ ይበልጥ የዲጂታል አገልገሎቶችን ተጠቃሚ እንዲሆን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚፈጥር ገልፀዋል፡፡

“ከዳሸን ባንክ ጋር በመጣመር የተለያዩ የዲጂታል አገልግሎቶችን ለማቅረብና ይህን መሰል የክፍያ አማራጭ ለንግዱ ማህበረሰቡና ሌሎች ደንበኞች ተጠቃሚ እንዲሆኑ በማስቻላችን ትልቅ ክብር ይሰማናል” ብለዋል፡፡

በዳሸን ቅድመ ክፍያ ማስተርካርድ ደንበኞች ከኤቲኤም እና ፖስ በተጨማሪ በኢ-ኮሜርስ ክፍያ መክፈል የሚያስችላቸው ሲሆን ደንበኞች ፕላስቲክ ወይም ቨርቹዋል ካርድ በመውሰድ መጠቀም ይችላሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ፕላስቲክ ካርዱ ስም የታተመበትና ስም ያልታተመበት የካርድ አይነቶችን የያዘ ነው፡፡

ደንበኞች ዳሸን ማስተር ካርድ ላይ የተሞላው የውጪ ምንዛሬ ሲያልቅ እንደገና በመሙላት መጠቀም የሚያስችላቸው ሲሆን ካርዱን ኤቲኤምና ፖስ ማሽን ላይ በማስገባት ወይም ያለ ንክኪ ገንዘብ ማውጣት ወይም ክፍያ መፈፀም  ያስችላቸዋል፡፡

ፕላስቲክ ካርዱ በሚስጢር ቁጥር የተጠበቀ ሲሆን ቨርቹዋል ካርዱ ደግሞ በአንድ ጊዜ የይለፍ ቃል ደህንነቱ የተጠበቀ ነው፡፡ ደንበኞች ካርዱን ለመጠቀም አቅራቢያቸው በሚገኝ የዳሸን ባንክ ቅርንጫፍ  ፓስፖርት፣ ቪዛ እና የበረራ ቲኬት በመያዝ አገልግሎቱን ማግኘት ይችላሉ፡፡

ዳሸን ባንክና ማስተርካርድ ከካርዱ በተጨማሪ የንግድ ተቋማት ክፍያቸውን በበይነ መረብ ከየትኛውም የአለም ክፍል መቀበል የሚያስችል የማስተርካርድ የክፍያ መቀበያ ማስተርካርድ ጌትዌይ/ MasterCard Payment Gateway System/ አስተዋውቀዋል፡፡

ይህ የማስተርካርድ ጌትዌይ/ MasterCard Payment Gateway System/ ሦስት የካርድ አይነቶችን በመቀበል የተሻለ የአገልግሎት አማራጭ መሆኑ ተመልክቷል፡፡

ይህም ለንግድ ተቋማት ክፍያ ለመቀበል እና ሽያጭ ለማከናወን  ለምግባረ ሰናይ ድርጅቶች እርዳታ እና የአባልነት ክፍያ ለመሰብሰብ እና ለሌሎች አገልግሎቶች ዘመናዊ የክፍያ መፈጸሚያ መስመር ነው፡፡

 

 

(more…)

Ecobank and Dashen Bank launch remittance app targeting Ethiopians in the Diaspora

Ecobank and Dashen Bank launch remittance app targeting Ethiopians in the Diaspora

Ecobank and Dashen Bank launch remittance app targeting Ethiopians in the Diaspora

Addis Ababa, 08 June 2023 – Ecobank, the leading Pan-African Banking Group, through its representative office in Ethiopia, has partnered with Ethiopia’s Dashen Bank to enable Ethiopians living in the diaspora, specifically Europe, to send money instantly to any Dashen Bank account, other local bank accounts, mobile money wallet and cash pick up using Ecobank’s Rapidtransfer International app (RTI). The cross-border remittance solution app which is available in the rest of Ecobank’s 33 countries, enables the African diaspora residing in Europe to remit funds back to Ecobank countries in Africa, including Ethiopia seamlessly.

Dr. James Kanagwa, Ecobank Ethiopia Country Representative, said: “As the bank with the largest geographical footprint across Africa and a recognized leader in digital, mobile, and borderless banking, we are delighted to partner with Dashen Bank to empower Ethiopians living in the European-based diaspora countries such as the United Kingdom, France, Italy, the Netherlands and 21 other European countries with access to our Rapid Transfer International app which enables Africans in Europe to send money back home affordably, instantly and securely.”

The Rapid Transfer International app is secure, easy to onboard, and navigates with user-friendly features such as multi-lingual options. Users will know the transparent foreign exchange rate prior to making a transaction and can choose to send funds directly to Dashen Bank accounts, wallet, cash-pick up, and same-day delivery to other commercial bank accounts.

According to Asfaw Alemu, Chief Executive Officer of Dashen Bank, “Our partnership with Ecobank enables us to reach out to the Ethiopian diaspora in Europe to provide them with a new, reliable, low-cost and convenient way to send money to their families and relatives back home in Ethiopia through the Rapid Transfer International app.”

In 2017, it was estimated that the Ethiopian Diaspora comprised a significant population of at least two million individuals, primarily residing in Europe and North America. According to Knomad, the global knowledge partnership on migration and development, remittance inflows into Ethiopia amounted to US$436 million in 2021 and an estimated US$327 million in 2022 – a figure that the partnership between Ecobank and Dashen Bank seeks to tap into by rolling out the Rapid Transfer International App. Users of RTI are able to send money back home at an average fee of 1.5 percent of the funds being remitted, making the Ecobank and Dashen Bank partnership the best remittance solution for the African diaspora to send more money back home to support their loved ones, build capital and accelerate financial inclusion for inclusive prosperity.

 

(more…)

ለዳሸን ባንክ አ.ማ ባለአክስዮኖች በሙሉ

ለዳሸን ባንክ አ.ማ ባለአክስዮኖች በሙሉ

ለዳሸን ባንክ አ.ማ ባለአክስዮኖች በሙሉ

የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አስመራጭ ኮሚቴ የዕጩ አባላትን ጥቆማ ከመጋቢት 23 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እየተቀበለ መሆኑ ይታውቃል። ስለሆነም ለባንኩ ዳይሬክተሮች ቦርድ አባልነት መስፈርቱን የሚያሟሉ ዕጩዎችን እስከ ሰኔ 23 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ መጠቆም የምትችሉ ሲሆን ስለተጠቋሚዎች መስፈርት እና ሌሎች ዝርዝር መረጃዎች ከባንኩ ድረ-ገፅ www.dashenbanksc.com እንዲሁም መጋቢት 20 ቀን 2015 ዓ.ም ከወጡት ሪፖርተር አማርኛው እና አዲስ ዘመን ጋዜጦች ማግኘት የሚቻል መሆኑን እየገለፀ፤ የጥቆማ ማቅረቢያ ቅፁን ከሁሉም የባንኩ ቅርንጫፎች፤ ከባንኩ ዋና መ/ቤት የዳይሬክተሮች ቦርድ አስመራጭ ኮሚቴ ጊዜያዊ ጽ/ቤት እና ከባንኩ ድረ ገፅ ማግኘት የሚቻል መሆኑን በአክብሮት ያሳውቃል፡፡

ማሳሰቢያ፡ የጥቆማ መስጫ ወረቀቱ በፖስታ ታሽጎ በአቅራቢያ ላሉ የባንኩ ቅርንጫፎች ወይም ባንኩ ዋና መስሪያ ቤት 14ተኛ ፎቅ ላይ ለሚገኘው የአስመራጭ ኮሚቴው ጊዜያዊ ፅ/ቤት ሊመለስ የሚገባ ሲሆን ከሰኔ 23 ቀን 2015 ዓ.ም በኋላ ጥቆማ ለማቅረብ የሚቀርብ ጥያቄም ሆነ ከዚህ ጊዜ በኋላ ባንኩ ጋር የሚደርስ የጥቆማ መስጫ ወረቀት ተቀባይነት የሌለው መሆኑን በአክብሮት ያሳውቃል፡፡

ለዳሸን ባንክ አ.ማ ባለአክስዮኖች

ለዳሸን ባንክ አ.ማ ባለአክስዮኖች

ለዳሸን ባንክ አ.ማ ባለአክስዮኖች

ዕጩ ዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ጥቆማ ከመጋቢት 23ቀን 2015 ዓ.ም እስከ ሰኔ 23ቀን 2015ዓ.ም ድረስ የሚከናወን ስለሆነ የጥቆማ ፎርሙን ከሁሉም የዳሸን ባንክ ቅርንጫፎች ወይንም ከስር ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ጥቆማ እንድታቀርቡ እናሳውቃለን፡፡

የጥቆማ ፎርም

የጥቆማ ፎርም

 

Facebook
Twitter
YouTube
LinkedIn
Instagram
Telegram