Jan 6, 2026
Dear the Winning MIDROC Investment Group Team,
On behalf of the entire family of Dashen Bank, S.C. I would like to extend my warmest congratulations to MIDROC Investment Group on the landmark announcement of bringing the globally renowned Carrefour brand to Ethiopia through Queens Supermarket.
We also take this opportunity to warmly welcome M/s Carrefour to Ethiopia and commend its decision to enter the market through a visionary and dedicated partner that demonstrates long term commitment to the country’s economic development, modern retail transformation and integration into global value chains.
This strategic partnership represents, we believe, a major milestone for Ethiopia’s modern retail sector and reflects MIDROC’s long standing commitment to introducing global standards, strengthening domestic supply chains and enhancing consumer access to quality and affordable products. We particularly commend MIDROC’s past proven role in stabilizing prices and availing fresh agricultural products delivery from farm gates- an intervention that has delivered tangible benefits to millions of Ethiopians at large and supported local producers in particular.
As Dashen Bank, we are proud to have the privilege of serving MIDROC Investment Group as a valued customer. We firmly believe that this partnership with Carrefour will generate meaningful and lasting impact across the economy, create employment opportunities, strengthen market competitiveness and further advance inclusive and sustainable growth in Ethiopia.
Once again, congratulations on this visionary achievement. We look forward to seeing the positive transformation this collaboration will bring to the retail landscape and wider community.
𝗔𝘀𝗳𝗮𝘄 𝗔𝗹𝗲𝗺𝘂
𝗖𝗘𝗢
𝗗𝗮𝘀𝗵𝗲𝗻 𝗕𝗮𝗻𝗸 𝗦𝗖
(more…)
Jan 5, 2026
በዳሸን ባንክ የኢኖቬሽን ወር በይፋ ተጀመረ

በዳሸን ባንክ በየአመቱ የተለያዩ ከፈጠራ ጋር የተያያዙ መርሃ ግብሮች የሚከናወኑበት የኢኖቬሽን ወር ዛሬ በይፋ ተጀምሯል።
በባንኩ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ዛሬ የኢኖቬሽን ወር ሲጀመር ተገኝተው ንግግር ያደረጉት ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ አስፋው ዓለሙ የባንኩ ሰራተኞች ይህ ወር ለፈጠራ ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳዩበት መሆኑን አመልክተው ፈጠራ በጊዜ የታጠረ አለመሆኑንና ሁሌም ተግባራዊ መደረግ ያለበት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የባንኩን አጠቃላይ አሰራሮች በተለይም የደንበኞችን አገልግሎት ይበልጥ ለማዘመን የሚያስችሉ የፈጠራ ስራዎችን በውስጥ የሰው ሃይል እንዲተገበሩ በማድረግ ለወደፊት በኢንዱስትሪው ይበልጥ ተወዳዳሪ መሆን እንደሚቻል አቶ አስፋው አስገንዝበዋል፡፡
ሁሉም የባንኩ ሰራተኞች በተለይም የወደፊቱ የባንኩ ተረካቢ የሆኑ ወጣቶች ይህን አጋጣሚ በመጠቀም ያሏቸውን የፈጠራ ሃሳቦች እንዲያቀርቡ ዋና ስራ አስፈፃሚው ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በጉባኤው ላይ የባንኩ የተለያዩ መምሪያዎች የስራ ሃላፊዎች የተሳተፉበት የፓናል ውይይት የተካሄደ ሲሆን በፈጠራ ምንነትና በደንበኞች አገልግሎት እንዲሁም ሌሎች የባንክ አገልግሎቶችን ለማዘመን በሚኖረው አስተዋፅኦ ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሂዷል፡፡
በፈጠራ ወር እ.ኤ.አ እስከ ጥር 15 ቀን 2026 ድረስ የተለያዩ የፈጠራ ሃሳቦች በባንኩ ሰራተኞች ቀርበው አሸናፊዎቹ ሽልማት ይበረከትላቸዋል፡፡
\

፡
(more…)
Jan 3, 2026
የዳሸን ባንክ 30ኛ ዓመት የምስረታ በዓል መከበር ጀመረ

የዳሸን ባንክ 30ኛ ዓመት የምስረታ በዓል መከበር ጀመረ
ከ30 ዓመት በፊት አሥራ አንድ ቅርንጫፎችን በአንድ ጀንበር ከፍቶ ሥራ በማስጀመር በኢትዮጵያ የፋይናንስ ኢንዱስትሪ ውስጥ የራሱን አሻራ ያሳረፈው ዳሸን ባንክ የምስረታ በዓሉን እኤአ ከጃንዋሪ 1 ቀን 2026 ጀምሮ ጀምሮ ለሚቀጥሉት ሶስት ወራት በተለያዩ ኹነቶች ማክበር ጀመረ፡፡
ዳሸን ባንክ የሦስት አሥርት ዓመታትን ያልተቋረጠ ስኬት ለሚዘክርበት ለዚህ በዓል የባንኩን ደንበኞች፣ ባለአክሲዮኖች፣የዳይሬክተሮች ቦርድና የማኔጅመንት አባላት፣ አጋር ተቋማትንና እንዲሁም ታታሪ ሰራተኞቹን እንኳን አደረሳችሁ ይላል፡፡
የዳሸን ባንክ የምስረታ በዓልን በማስመልከት መልዕክት ያስተላተላለፉት የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ዓለሙ “እንኳን ለዳሸን ባንክ 30ኛ ዓመት የምስረታ በዓል አደረሳችሁ፤ዳሸን በኢትዮጵያ ገናና መለያ (ብራንድ) ባለቤት የኾነው ከምንም ተነስቶ በአጋጣሚ አይደለም ፡፡ዘመንን የሚሻገር ራዕይ የነበራቸው አሥራ አንድ መስራቾቹ በኢትዮጵያ እንደ ራስ ዳሸን ተራራ በሩቁ የሚታይ ትልቅ የፋይናንስ ተቋም ለመመሥረት በነበራቸው ቀና ፍላጎትና ፅኑ ዓላማ የተነሳ ነው ፡፡” ብለዋል፡፡
አቶ አስፋው አክለውም፣ ከጃንዋሪ 1 ቀን 2026 ጀምሮ ለሚቀጥሉት ተከታታይ ሦስት ወራት፤ ዳሸን ባንክ የፋይናንስ ኢንዱስትሪውን ለማዘመን የነበረውን ፋና ወጊ ሚና፣ ለደንበኞቹ የገባውን ቃልኪዳን በመጠበቅ እንዲሁም በሦስት አሥርት ዓመታት ውስጥ ባንኩ ያለፈባቸውን ሂደቶች በማስታወስና በሁሉም መስክ ደማቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱትን የቀደሙ ባለውለታዎቹን በሚዘከሩ የተለያዩ ኹነቶች ያከብራል ፡፡
በ11 ባለአክሲዮኖች የተቋቋመው ዳሸን ባንክ በዚህ ወቅት የባለአክሲዮኖቹ ቁጥር 4,974 የደረሰ ሲሆን፣ በአስራ አንድ ቅርንጫፎች የተጀመረው የባንኩ አገልግሎት አሁን ላይ በ906 ቅርንጫፎች እየተሰጠ ይገኛል፡፡ የባንኩ የተከፈለ ካፒታል ከ14.9 ሚሊዮን ብር ተነስቶ በዚህ ወቅት 14.3 ቢሊዮን ብር ሆኗል ፡፡
የዳሸን ባንክ የተጠናቀቀው የበጀት ዓመት (2017) የፋይናንስ አፈጻጸም ሪፖርት እንደሚያሳየው የባንኩ ጠቅላላ ሃብት ከ254 ቢሊዮን ብር በላይ የተሻገረ ሲሆን፣ የተቀማጭ ገንዘብ መጠኑ ደግሞ 202.2 ቢሊዮን ብር ሆኗል፡፡ በተጨማሪም የዳሸን ባንክ የደንበኞቹ ቁጥር ከስምንት ሚሊዮን በላይ ደርሷል፡፡
ለሚቀጥሉት ሶስት ወራት በተለያዩ ኹነቶች የሚከበረው የዳሸን ባንክ 30ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ባንኩ በኢትዮጵያ የፋይናንስ ኢንዱስትሪ ያለውን አበርክቶ በሚዘክሩ የተለያዩ ኹነቶች ይከበራል ፡፡
(more…)