Press Releases

ዳሽን ባንክና ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ያስገነቡት የምገባ ማዕከል ተመረቆ ሥራ ጀመረ ዳሽን ባንክና ሜድሮክ ኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጋራ በመተባበር በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ቦሌ አራብሳ ኮንዶሚኒየም አካባቢ በ25 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነቡት ተስፋ ብርሃን አሙዲ 3ኛ ቅርንጫፍ የምገባ ማዕከል የካቲት 24 ቀን 2015 ዓ.ም በይፋ ተመርቆ ሥራ ጀምሯል፡፡ በምርቃው ሥነ-ስርዓት ላይ...

ዳሸን ባንክ በቴክኖሎጂ የታገዘ የዱቤ ግብይት አስተዋወቀ
(አዲስ አበባ፡ ታህሳስ 25፤2015) ዳሸን ባንክ በቴክኖሎጂ የታገዙ አገልግሎቶችን በማስተዋወቅ በሚሊየን የሚቆጠሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የባንክ አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ባንኩ አዳዲስ አገልግሎቶችን የማስተዋወቅ ጥረቱን በመቀጠል አሁንም ከኤግል ላየን ቴክኖሎጂስ ጋር በመተባበር የቆየውን የማህበረሰባችንን የዱቤ ግብይት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እና አስተማማኝ የባንክ አሰራር በማገዝ ዱቤ...

የስብሰባ ጥሪ! ለዳሸን ባንክ አ.ማ. ባለአክስዮኖች በሙሉ!
የዳሽን ባንክ አ.ማ. ባለአክሲዮኖች ሃያ ዘጠነኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ጥቅምት 17 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ በሸራተን አዲስ ሆቴል ስለሚካሄድ ባለአክሲዮኖች ወይም ወኪሎቻቸው በተጠቀሰው ቀን፤ ሰዓት እና ቦታ በስብሰባው ላይ እንዲገኙ የዳይሬክተሮች ቦርድ ጥሪውን ያቀርባል፡፡ Read More…

ዳሸን ባንክና የጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ
(ጋምቤላ፣ ነሐሴ 27 ቀን 2014 ዓ.ም) ዳሸን ባንክና የጋምቤላ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በጋምቤላ ክልል የቢዝነስ ስራዎችን ለማስፋት እና ማህበረሰብ ተኮር ፕሮጀክቶችን ለመደገፍ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል፡፡ ዳሸን ባንክ በክልሉ ለሚገኙ አነስተኛና ጥቃቅን ተቋማት ብድር እንዲዉል ለክልሉ ማይክሮፋይናስ ተቋም 25 ሚሊየን ብር በአነስተኛ ወለድ በክልሉ መንግስት ዋስትና...

ምርጥ አስሮችን ለመምረጥ የሚካሄደው ውድድር ዛሬ ነሐሴ 23 2014 ዓም በዳሸን ባንክ ዋናው መ/ቤት ተጀምሯል።
ከተለያዩ ከተሞች ከተውጣጡ ሰላሳ አምስት ተወዳዳሪዎች ውስጥ ምርጥ አስሮችን ለመምረጥ የሚካሄደው ውድድር ዛሬ ነሐሴ 23 2014 ዓም በዳሸን ባንክ ዋናው መ/ቤት ተጀምሯል። ከሀዋሳ፣ ከድሬደዋ፣ ከአዳማ፣ ከደሴ እና ከባህርዳር የስልጠናና የውድድር ማዕከላት የተውጣጡ የስራ ፈጠራ ተወዳዳሪዎች ወደ ምርጥ አስር ለመግባት ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ። በዚህ ውድድር ለሀገር እና ለወገን ጠቃሚ እንዲሁም ችግር ፈቺ የሆኑ የስራ...

Dashen Bank Chooses IBM Hybrid Cloud Solutions to Accelerate Digital Transformation to Meet Growing Digital-First Customer Needs
Dashen Bank is collaborating with IBM to modernize its cloud integration architecture. The implementation enables Dashen Bank to enhance open banking experiences with fintechs, neo-banks and corporate and telecom partners to improve customer experiences. Addis Ababa,...

ኢትዮ ቴሌኮም ከዳሽን ባንክ ጋር በአጋርነት የቴሌብር የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎቶችን በዛሬው ዕለት አስጀመረ
ቴሌብር የአገልግሎት አድማሱን በማስፋት ለማህበረሰባችን በተለይም በዋናነት መደበኛ የፋይናንስ አገልግሎት ተጠቃሚ ላልሆነው የማህበረሰብ ክፍል ሁለንተናዊ ለውጥና መሻሻል ከፍተኛ ሚና ያላቸውን፣ እንዲሁም የፋይናንስ አገልግሎት ከማግኘት ባሻገር ትርጉም ያለው ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ የሞባይል አነስተኛ ብድር፣ የኦቨርድራፍትና የቁጠባ አገልግሎቶችን ከዳሽን ባንክ ጋር በአጋርነት መስጠት እንዲችል እ.ኤ.አ ነሐሴ 01 ቀን...

ዳሸን ባንክ እና ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ከአዲስ አበባ መስተዳደር ጋር በመተባበር በልደታ ክ/ከተማ ያስገነቡትን ሁለተኛውን የምገባ ማዕከል ዛሬ ሐምሌ 13 ቀን 2014 ዓ.ም በይፋ አስመረቁ።
የምገባ ማዕከሉ በከተማዋ ውስጥ ላሉና በቀን አንድ ጊዜ እንኳን መመገብ ለማይችሉ ወደ 3 ሺህ ለሚጠጉ ዜጎች ጤናውን የጠበቀ ምግብ እንዲያገኙ የሚያግዝ ሲሆን ከዚህ ቀደም በከተማው አስተዳደር ውስጥ ከሚገኙት ጋር ተጨምሮ በጠቅላላው ሰባተኛው የምገባ ማዕከል ይሆናል፡፡ አጠቃላይ የግንባታ ወጪው 40 ሚሊዮን የተገመተው ይህ የምገባ ማዕከል ሙሉ ወጪውን ዳሸን ባንክ ከሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ጋር በመተባበር የሸፈኑት ሲሆን፣...

ዳሸን ባንክ ዘመናዊ የመረጃ ማዕከል አስመረቀ
(ሰኔ 16 /2014፣ አዲስ አበባ) በኢትዮጵያ የባንክ አገልግሎት ታሪክ ውስጥ የአዲስ ዘመን ጅማሮ ተደርጎ ሊወሰዱ የሚችሉትን የኤሌክትሮኒክ ክፍያ እና የሞባይል ካርድ አገልግሎቶች በማስተዋወቅ ረገድ ፈር ቀዳጅ የሆነው ዳሸን ባንክ፣ ዘመናዊና በግል የፋይናንስ ተቋም ደረጃ የመጀመሪያ የሆነውን Tier III የመረጃ ማዕክል አስመረቀ፡፡ የመረጃ ማዕከሉ ከፍተኛ ኃይል ያላቸውን ከ1,000 ያላነሱ ሰርቨሮችና ሌሎች ተያያዥ...

የዳሸን ባንክ ሁለተኛው ዙር የስራ ፈጠራ ስልጠናና ውድድር መርሃግብር አካል የሆነ የአቅም ግንባታ ስልጠና በድሬዳዋ ከተማ ተደረገ።
ለአምስት ተከታታይ ቀናት በሚቆየው ስልጠና ከተለያዩ አካባቢዎች የተውጣጡ ሰልጣኞች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡ ሰልጣኞቹ በስኬታማ ስራ ፈጣሪዎች ባህሪያት፣ በንግድ ስራ ዕቅድ አዘገጃጀት፣ በጊዜ አጠቃቀም፣ አነስተኛ ድርጅቶችን በማስተዳደር ክህሎት፣ በግለሰብ ገንዘብ አስተዳደር፣ በድርጅት ገንዘብ አስተዳደርና በባንክ አገልግሎት ዙሪያ ያተኮረ ስልጠና ወስደዋል፡፡ ዳሸን ባንክ በድሬዳዋ ከተማ ለሥራ ፈጣሪዎች ሲሰጥ የቆየውን ሥልጠና...